Saturday, January 5, 2013

እነዚህን አንብባችኋቸዋል?

በዚህ ጦማር ላይ ከጻፍኩ ሰነበትኩ:: ነገር ግን ብዙዎቻችሁ እንደምታውቁት የጠፋሁት መጻፍ እርም ብዬ ሳይሆን ዞን ዘጠኝ ላይ መጻፍ በመጀመሬ ነው:: ታዲያ ምናለ ይሄንን subscribe አድርገው ዞን ዘጠኝን ያላደረጉ ካሉ ቢያነቡኝ ብዬ ጥቂቶቹን እንዲህ ዘረዘርኳቸው:: እንዳሻችሁ አድርጓቸው::


15. የሥርዐት ለውጥ እና ሃይማኖቶች

14. ለውጥን መቋቋም እና መፍራት

13. አብዮት ወይስ አዝጋሚ-ለውጥ?

12. ግልጽ ደብዳቤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ

11. በኢትዮጵያ የቡድን አመራር ተጀምሯል?

10. የጉዞ ማስታወሻ፤ ሥልጣኔ ወደላይ እና ወደታች

9. የጉዞ ማስታወሻ፤ መቐለን በአንድ ቀን

8. ኢሕአዴግ ሥልጣኑን በምርጫ ይለቃል?

7. ጠንቅቆየመጻፍና አለመጻፍ ጉዳይ

6. የእነርሱ እና የእኛ ሕዳሴ

5. የታክሲ ሰልፍ መጀመሪያውና መጨረሻው

4. ‹‹ሕዝብ›› ምንድን ነው?

3. የትችት ባሕላችንን ብንተቸውስ?

2. ይቅርታ የሚገባው የኢትዮጵያ ሕዝብ!

1. አራማጅነትበኢትዮጵያ



Thursday, November 8, 2012

የአዲስ አበባ ከተማ እና ምርጫዋ


አዲስ አበባ 125ኛ ዓመቷን እያከበረች ነው፡፡ በከተማይቱ ልደት ሰሞን እናትና አባቷ (በመናገሻ ከተማነት የቆረቆሯት አጤ ምኒልክ እና ስሟን ያወጡለት እቴጌ ጣይቱ) ስማቸው ሲነሳ አልሰማሁም፡፡ ይልቁንም ላለፉት 21 ዓመታት በፌዴራል መንግሥቱ ርዕሰ መሪነታቸው በእጅ አዙር የዘወሯት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ስም በተደጋጋሚ ሲነሳ እና በየመንገዱ ዳር በቆሙ ‹ቢልቦርዶች› ላይ ከከተማይቱ የመሠረተ ልማት አውታሮች ፎቶ ፊት ለፊት በጉልህ በተቀመጡ ምስሎቻቸው ታጅቦ ታይቷል፡፡

የክብረ በዓሉን ክንውን እንዲያዘጋጅ የኢሕአዴግ ሰዎች የሚመሯቸው ዋልታ እና ፋና ጥምር-ድቅል የሆነው ዋፋ የማስታወቂያ ድርጅት ሙሉ ኃላፊነቱን ወስዷል፡፡ ምናልባትም የዚሁ የፓርቲ ጥገኝነት ጉዳይ ይሆናል መለስን በግምባር ቀደምነት የከተማይቱን ቆርቋሪ አስዘንግቶ ያስጠቀሳቸው፡፡

ለነገሩ ይህን ጽሑፍ ለማሰናዳት ያነሳሳኝ የክብረ በዓሉን ዐብይ-ሰብ (figure) ለመሰየም አይደለም፡፡ ስለከተማይቱ እያነሳሁ ይህንን ያፈጠጠ ስህተት ሳልነቅስ ማለፍ ስላልሆነልኝ ነው፡፡ የጽሑፌ ርዕሰ ጉዳይ ሚያዝያ ወር ላይ የሚካሄደው ምርጫ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ምርጫ ከሀገር አቀፍ ምርጫ በሁለት ዓመት እንዲዘገይ የሆነው፣ በምርጫ 97 ከአንድ ወንበር በስተቀር ሁሉንም የከተማዋን ምክር ቤት መቀመጫዎች አሸንፎ የነበረው ቅንጅት ምክር ቤቱ ለመግባት ባለመፍቀዱ  ማሟያ ምርጫ እስኪካሄድ በተፈጠረው መዘግየት ሳቢያ ነው፡፡

ሀገሪቱ ከአንድ ጠቅላይ ሚኒስትር በላይ ባላየችባቸው ሁለት ዐሥርት ዓመታት ውስጥ፣ አዲስ አበባ አምስት ከንቲባዎችን ለማየት ታድላለች፡፡ አንዴ ግዜያዊ የባለአደራ ከንቲባ ስታስተናግድ ቀደም ብሎ ደግሞ ‹‹ተበለሻሸች›› ተብሎ - የጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣን በሚፈቅደው መሠረት - ምክር ቤቷ ፈርሶ በድጋሚ እንዲገነባ ተደርጎ ነበር፡፡ በነዚህ ጊዜያት ከተሠሩ ሕንፃዎች እና መንገዶች በተጨማሪ በተለይ ሕዝቡን ያማከለ ሥራ የሠሩት አርከበ ናቸው፡፡ አርከበ የኮንዶሚኒዬም ቤቶችን እና አርከበ ሱቆች ተብሎ በማኅበረሰቡ የተሰየሙላቸውን ጥቃቅን እና አነስተኛ ንግድ ቤቶች ያስጀመሩ ከንቲባ ናቸው፡፡

በዐሥር ክፍለከተሞችና ከ100 በላይ በሆኑ ቀበሌዎች (አሁን ወረዳዎች) የተከፋፈለችው አዲስ አበባ ከ5 እስከ 7 ሚሊዮን የሚደርሱ ነዋሪዎች እየዋሉ እንደሚያድሩባት ይገመታል፡፡ ከነዚህ ውስጥ የነዋሪነት መታወቂያ ያላቸው ከ3 ሚሊዮን አይበልጡም፡፡ ለምርጫ ብቁ የሆኑት ደግሞ 2.2 ሚሊዮን የሚጠጉት ብቻ ናቸው፡፡

Monday, October 15, 2012

የኛ ኃይል



ዞን ዘጠኝ የተወሰደ


“ፒያሳ፤ መሐሙድጋ ጠብቂኝ” በመሐመድ ሰልማን የተጻፈ እና ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈ ኢ-ልቦለዳዊ መጣጥፎች ስብስብ ነው፡፡ የዛሬ ዓመት ገደማ ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ በተባለ መንግስታዊ ባልሆነ ድርጅት  አማካይነትመጽሐፉን የመገምገሚያ ዝግጅት አምስት ኪሎ በሚገኘው ብሔራዊ ሙዚዬም ቀርቦ ነበር፡፡ በውይይቱ መሐል የመጽሐፉ ዝነኝነት ምንጮች ምን ምን ናቸው የሚል ውይይት የነበረ ሲሆን ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ‹‹ደራሲው የአዲስ ነገር ጋዜጣ ጸሐፊ የነበረ›› መሆኑን እና ‹‹ጽሑፎቹም በአዲስ ነገር ጋዜጣ እና ድረገጽ ላይ ወጥተው የነበሩ›› መሆናቸውን ጠቀሰ፡፡ ውይይቱ የአዲስ ነገር ጋዜጣ መታሰቢያ ይመስል፣ የትዝታ ጫወታው ተጧጧፈ እናም ከውይይቱ ተሳታፊዎች አንዱ የሚከተለውን ሲናገር ረዥም ጭብጨባ አዳራሹን አደመቀው ወጣቱ አስተያየት ሰጪ በንግግሩ መሃል የተጠቀመው እና ጢም ብሎ የሞላውን አዳራሽ በጭብጨባ ያናጋው ንግግር የሚከተለው ነበር፡፡

‹‹ይህ ትውልድ በአዲስ ነገር ጋዜጣ የሚደራደር ትውልድ አይደለም፡፡››

ጉዳዩን አስገራሚ የሚደርገው ወጣቱ ይህንን የተናገረው አዲስ ነገር ጋዜጣ መታተም ካቆመች ከሁለት ዓመታት በኋላ መሆኑ ሲሆን፣ አጋጣሚው የጋዜጣዋ መንፈስ በበርካቶች ልብ ውስጥ በትኩስነት መኖሩን የሚናገር ነበር፡፡

ዛሬ፣ ጥቅምት 5/2005 የዓለም የጡመራ የተግባር ቀን (Blog Action Day 2012) “የኛ ኃይል” በሚል መሪ ቃል ይከበራል፡፡ የጡመራ የተግባር ቀን በየዓመቱ የሚከበር፣ በዓለም ዙሪያ ያሉ ጦማሪዎች በሙሉ በአንድ ሐሳብ ዙሪያ የሚጽፉበት ቀን ነው፡፡ የተጀመረው እ.ኤ.አ. በ2007 ሲሆን በተመሳሳይ  ዓመት ‹‹አካባቢ››፣ በ2008 ‹‹ድህነት››፣ በ2009 ‹‹አየር ለውጥ››፣ በ2010 ‹‹ውሃ››፣ በ2011 ‹‹ምግብ›› በሚል ሲካሄድ ዘንድሮ ደግሞ በ2012 ‹‹የእኛ ኃይል›› በሚል እየተካሄደ ይገኛል፡፡

የዘንድሮው መሪ ቃል፣ ማኅበረሰብ፣ እኩልነት፣ ፀረ-ሙስና እና ነጻነትን በተመለከተ የኛ ኃይል ምን እንደሆነ በመስበክ እንዲከበር ታስቦ የተመረጠ ነው፡፡ አከባበሩ ቀላል ነው፤ አስተባባሪዎቹ እንዳስቀመጡት ‹‹profile someone or a group who inspires you by the way they made a positive influence… (ባመጡት አዎንታዊ ተጽዕኖ ያነቃቃችሁን የሆነ ሰው ወይም ቡድን በመምረጥ ጻፉ…)›› የሚል ነው፡፡

እኛም ጮክ ብለን ስናስብበት እና በጭንቅላታችን ያቃጨለችው አዲስ ነገር ጋዜጣ ብቻ ሆነች፡፡ አዲስ ነገር ጋዜጣ ለሁለት ዓመታት (ከጥቅምት 2000 እስከ ታሕሳስ 2002) ብቻ በስርጭት የቆየች ነገር ግን መራኄ አዘጋጇ መስፍን ነጋሽ የጋዜጣዋን ሁለተኛ ዓመት አስመልክቶ እንደገለፀው ‹‹አጭር ግን ረዥም ዓመት›› የኖረች ያክል የማትረሳ ጋዜጣ ናት፡፡

Tuesday, October 9, 2012

የኃይለማርያም ፲ ተግዳሮቶች



የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ኅልፈት ከተሰማ 50 ቀናት ሆኑት፤ አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ቃለ መሓላ ከፈፀሙ ደግሞ 18 ቀናት፡፡ እነዚህ ከሁለት ሳምንታት እምብዛም ያልበለጡ ቀናት የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያምን አያያዝ ለመገምገም በቂ አይደሉም ነገር ግን ‹‹ያባት ዕዳ ለልጅ›› በሚለው ብሒል መሠረት የመለስን ፈለግ በመከተል እና ባለመከተል መካከል፣ ሊያመጧቸው በሚችሏቸው ለውጦች እና ሕዝብ/አገር ከሚጠብቅባቸው ነገሮች አንፃር የሚጠብቃቸውን ተግዳሮት ማስቀመጥ ይቻላል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም በተለይ ከቪኦኤ የእንግሊዝኛው አገልግሎት ጋር ባደረጉት የ40 ደቂቃ ቃለምልልስ፥ ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር የተለየ አቋም እንደሌላቸው መታዘብ ይቻላል፡፡ ፓርቲውም ቢሆን የአቶ መለስን ውርስ ለማስቀጠል እንደሚተጋ በተደጋጋሚ ተናግሯል፡፡ በተቃራኒው መለስ የሚባልላቸውን ያህል ውጤታማ እና ፍፁም አልነበሩም፡፡ ለዚህም ምስክሩ ሳይዘጉ የተዉአቸው የሚከተሉት አጀንዳዎች ናቸው፡፡ የአቶ ኃይለማርያም ተግዳሮቶች ሁነው ይቀጥላሉ፡፡

Saturday, September 8, 2012

የ2004 ሒሳብ ሲዘጋ



እንዳለፉት ጊዜያት ሁሉ በዚህ ዓመትም ሰዎች ከፌስቡክ ውጪ እንዴት እንደሚኖሩ ለማወቅ ጉግል ውስጥ ፈልጌም፣ አስፈልጌም መልስ ማግኘት አልቻልኩም፡፡ ስለዚህ በፌስቡክ ውስጥ መኖሬን ቀጥያለሁ፡፡ በርግጥ ፌስቡክ ምንም አልጎደለበትም፤ እንኳን የሆነው የታሰበው ሳይቀር ይወራበታል፡፡ ለአብነትም የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትርን ሞት መጥቀስ ይቻላል፡፡

ፌስቡክ ምድር ላይ ካለው ‹እቤት-እመስሪያቤት› ምልልስ የተሻለ ፋይዳ ያለው ሥራ ለመስራት የተመቸ ዕድልም ይፈጥራል፡፡ የዳቦ ጉዳይ (bread winning) ሁላችንንም በየሙያችን ቢያሰማራንም፣ የምንናፍቀው እና የሚናፍቀን ሌላ ነገር የለም ማለት መቼም አይደለም፡፡ ኢትዮጵያውያን እርስ በእርስ የምንዋደደውን ያክል የምንወደውና የሚወደንን ዓይነት መንግስት ያገኘንበት ጊዜ እምብዛም ነው፡፡ ይህንን መናፈቅ እና መማከር ደንብ ሆኖ፣ በሌላም፣ ዓመቱን ሙሉ በጻፍናቸው ነገሮች ያስደሰትነው ሰው እንዳለ ሁሉ ያስቀየምነው የለም ማለት ዘበት ነውና፣ ያው የግል ጥቅም ይዞን አለመሆኑ ታውቆ በአዲስ ዓመት ዋዜማ ይቅር መባባልን የመሰለ ነገር የለም፡፡

በዚህ ዓመት በፌስቡክ ገጼ ላይ ያሰፈርኳቸውን እና ከወዳጆቼ ጋር ቅኔ የተዛረፍኩባቸውን ግጥሞች በአንድ መድብል ‹‹የፌስቡክ ትሩፋት›› በሚል ጠርዠዋለሁ፡፡ ማንም ቢፈልግ እዚያው ባለበት ማንበብ፣ ወይም ዳውንሎድ ማድረግ ይችላል፡፡ አምና ሁለት ሺህ ሦሰትን በአርባ ሁለት በሚል በ2003 የጻፍኳቸውን ጦማሮች አንድላይ ቢጠረዙ መልካም ነው በሚል ማስቀመጤ ይታወሳል፡፡ አሁንም ዘንድሮ የሞነጫጨርኳቸውን እዚህ አስቀምጫለሁ፡፡

በስህተቴ ያረማችሁኝን እና የነቀፋችሁኝን፣ በብርታቴ ላይ አበርታች የሆነ አስተያየታችሁን ለሰጣችሁኝ፣ በዝምታ ስታነቡኝ ከርማችሁ መንገድ ላይ ስታገኙኝ ለነገራችሁኝ እና ለሌሎቻችሁም ሁሉ ምስጋናዬ እንዲደርሳችሁ ከጉልበቴ ሸብረክ ማለቴን እንደምታስቡልኝ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡

አዲሱ ዓመት ሕልማችን የሚሞላበት፣ ለፍቅራችን ዋጋ የምንሰጥበት ይሁን፤ አሜን!

በ2004 የተጻፉ
  1. መንግስት ያልቻለውን እኛ ብንሞክረውስ?
  2. ሞክሮ መሳሳት እና ከስህተት መማር
  3. ፍቅር፤ ከፍቅር እስከ መቃብር (ልቦለድ)
  4. የአፋልጉኝ ማስታወቂያ ለተቃዋሚዎች
  5. የትራንስፎርሜሽኑ ዕቅድና አንዳንድ አካላት
  6. ኢትዮጵያውያን ለምን ዲቪ አይሞሉ?
  7. ደረሰኝ ሳይቀበሉ፥ ሒሳብ አይክፈሉ
  8. አሰብ የማን ናት?” በጨረፍታ
  9. ይህ - የታገልንለትን ጉዳይ አለማወቅ ነው
  10. አዎንታዊ ሀቆች ስለሊቢያ እና ጋዳፊ (Positive facts about Libya and Gadaffi) (ፌስቡክ ላይ ብቻ)
  11. ኢትዮጵያ ከኢሕአዴግ በኋላ፤ ሰጥቶ የመንጠቅ ዘመነ መንግስት
  12. In T1me - ጊዜ ገንዘብ (ገንዘብ ጊዜ) ቢሆን ኖሮ!
  13. “Every nation deserves its government” - ኦቶ ቮን ቢስማርክ
  14. የኢሕአዴግ ‹‹ትርፍ›› እና ኪሳራ
  15. ኢትዮጵያውያን፣ ኢትዮጵያ እያለች ሃገር የላቸውም
  16. የዳዊት ከበደ እና የተመስገን ደሳለኝ ወጎች
  17. ጨርቆስና ቦሌ - ሕይወትን እኛ እንደኖርነው!
  18. እስኪ ስለዋጋ - ቆም ብለን እናውጋ!
  19. ገመና 2 ሰው ለሰው፣ ጀግንነትና ኢትዮጵያ
  20. ሰማንያ ሚሊዮን እስከምንደርስ እንታገላለን
  21. የፈረንጅ አምልኮ በኢትዮጵያ
  22. የኢትዮ ቴሌኮም ቁልቁለት
  23. አፍንጫ ሲመታ ዓይን አያለቅስም ወይ?
  24. የሐበሻ አምልኮ በኢትዮጵያ
  25. አማርኛ በመዝገብ ላይ
  26. የቫለንታይን ጉርሻ ለወንዶች፤ የአዲስ አበባ ሴቶችን እንደታዘብኳቸው - ልማላችሁ! (ፌስቡክ ላይ ብቻ)
  27. ኑሮ በአገርኛ÷ ጾም ይበዛበታል!
  28. የአሜሪካ ኮንግረስ እና ሌሎችም ከኢትዮጵያ ፓርላማ መማር የሚገባቸው!
  29. ሦስት ሰዓታትን በግዞት (ፌስቡክ ላይ ብቻ)
  30. እቴጌ ጣይቱ ብጡል እና እቴጌ አዜብ መስፍን
  31. እንደ እርሳቸው ያለ ፊትም አልነበረ፤ አሁንም የለ፤ ምናልባት፣ ምናልባት ወደፊት ሊኖር ይችላል!
  32. ሕዝቦች ግለሰብን ይጨቁናሉ!
  33. እውትምሰሚ ያጡ ድምፆች!’
  34. መራመድና ባሉበት መሽከርከር፤ ሁለት የኑሮ ፈሊጦች
  35. እስኪ እንጠያየቅ፤ አገራችን የት ነው? (መጠባበቂያ ካስፈለገ)
  36. የቴዲ አፍሮን አልበም ያልገዛሁባቸው 5 ምክንያቶች
  37. ደጉ ኢትዮጵያዊ፤ ከልብ ካለቀሱ እምባ እንደማይገድ ያስመሰከረ ስብስብ
  38. የኢትዮጵያ መንግስት መጠላቱን የሚያሳብቁ ምልክቶች
  39. ከአከሌን አሰሩት እስከ አከሌን አገዱት!
  40. አብዮት ወረት ነው!
  41. የጋንዲ፣ ኪንግ እና ማንዴላ መንፈስ
  42. ዴሞክራሲ ኢትዮጵያ ውስጥ አለ ወይስ የለም? (እርስዎ ምን ይላሉ?)
  43. የመፈረጅ ፍራቻ እና የመፈረጅ አደጋ
  44. 21 ዓመት በኋላ (ዴሞክራሲ ሲሰላ)
  45. አሸባሪፊልምም ይታገድ ጀመር (በነገራችን ላይ ከወራት በኋላ ድጋሚ ለአንድ ሳምንት እንዲታይ ተደርጓል)
  46. የአንድ ኪራይ ሰብሳቢ መንግስት ታሪክ
  47. እነአልበርት አይንስታይን ስለዘንድሮው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ምን ይላሉ?
  48. Hookah እና አሜሪካ
  49. የተመቻቸ ጊዜ መጠበቅ?
  50. አምስት የኢትዮጵያ ጠላቶች
  51. የባለፀጋዋን አገር ዜጋ፤ አቶ ድህነትን እናስተዋውቅዎ
  52. እውነቱ እና ፍርሃቱ
  53. የእንቆቅልሹ እንቆቅልሾች
  54. ጫወታ ስለየኦሎምፒክ ጫወታዎች
  55. ፋጡማ ኖረች አልኖረች፣ ጳጳሱ ኖሩ አልኖሩ…?
  56. የመለስ ሁለት መልክ
  57. ነውርን ማን ፈጠረው?
  58. በቁማቸው ከገደሉት በሞታቸው የገደሉት
  59. ኢሕአዴግ ቀይ እስክሪብቶ እኔ እንደወደድኩት (ዞን ዘጠኝ ላይ)
  60. ፎንቱ ፎኒፍ ሪፈታ ጄናን ኢቲሌን ጂቢቻ ካቴ(ዞን ዘጠኝ ላይ)
  61. የመለስ ዜናዊሀሁበስልጣን ጎዳና (ዞን ዘጠኝ ላይ)
  62. እውነት እና እስር ቤት (እስካሁን ለሰው ያላሳየሁት/ልቦለድ)

The Return to Rule by Law: The Case of Draft CSO Law in Ethiopia

(Befekadu Hailu) [The original version of this piece is written in Amharic; please read the Amharic version for accuracy.] The Ministry...