Thursday, February 21, 2013

#Ethiopia, #StopCensorship: ሐሳብን በነጻ መግለጽ በኢትዮጵያ - ሕገ መንግሥት ላይ እና በተግባር



በበፍቃዱ ኃይሉ

ሰሞኑ ‹‹የሕገ-መንግሥቱ›› ይከበር የበይነመረብ ዘመቻ 2ኛ ዙር በአንቀጽ 29 (ሐሳብንና አመለካከትን የመያዝና የመግለጽ መብት) ይከበር ዙሪያ በዞን ዘጠኝ አስተባባሪነት እየተካሄደ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ለዘመቻው ግብአት እንዲሆኑ አንዳንድ እውነታዎችን ስለሕገመንግሥቱ እና ስለቀደሙት፣ ስለአተገባበሩም ጭምር እነሆ፡-

ሐምሌ 30/1966 በንጉሡ ነገሥት መንግሥት ረቂቅ ሕገ-መንግሥት፡-

አንቀጽ 25/1

ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የሐሳብ ነፃነት አለው፡፡ ማናቸውንም ሐሳብ በንግግር፣ በጽሑፍ ወይም በሌላ ዘዴ የመግለጽና የማሰራጨት እንዲሁም ሌሎች የገለጹትን የማወቅ መብት አለው፡፡

አንቀጽ 25/2

ማንኛውም ሰው በቴሌፎን፣ በቴሌግራፍ፣ በፖስታ ወይም በማናቸውም ሌላ የመገናኛ ዘዴ ሚስጢሩ እንደተጠበቀ የመነጋገርና የመላላክ መብት አለው፡፡

ውንብድና እና የአዲስ አበባ ዝምታ…

  (በፍቃዱ ኃይሉ)  አዲስ አበባ ውስጥ ውንብድና ጨምሯል። ይህንን የምለው እንዲሁ በልምድ “ዛሬ ከትላንት ይከፋል” በሚል ዲስኩር ተጠልፌ አይደለም። በራሴ ደርሶ ስላየሁት ነው፤ ያውም በአንድ ዓመት ርቀት ውስጥ ሁለት ጊዜ...