Skip to main content

መራመድና ባሉበት መሽከርከር፤ ሁለት የኑሮ ፈሊጦች


ወ/ሮ ሙሉ፤ የኢትዮጵያ ንግድ ማሕበራትና ሴክቶራል አሶሲየሽን ፕሬዚዳንት - ልምዳቸውን እያጋሩ ነው፡፡ “ጣጣ” በማያውቀው አማርኛቸው የተራመዱበትን የሕይወት መንገድ (ልበለው ስኬት) ያወራሉ፣ ያወራሉ፤ እኔም አዳምጣለሁ፣ አዳምጣለሁ፡፡ በመሃል ‘ከራስ ጋር መወዳደር’ ስለሚባል ነገር አነሱና ተናገሩ፡፡ “መወዳደር ያለብን ከሰዎች ጋር ሳይሆን ከራሳችን ጋር ነው፣ እከሌ እንዲህ ስለሆነ እኔም መሆን አለብኝ ማለት የለብንም” አሉ፡፡ ተቀየምኳቸውና እርሳቸው ጨርሰው ታዳሚው ጥያቄ እንዲጠይቅ ዕድል ሲሰጠው እጄን ዘለግ አድርጌ አወጣሁ፡፡

“አነጋገርሽን ወድጄልሻለሁ፤” ብዬ ጀመርኩ፡፡ በነገራችን ላይ ወይዘሮዋ፣ የአራት ልጆች እናት ቢሆኑም፣ የ33 ዓመት የሥራ ልምድ ቢኖራቸውም ዕድሜያቸውን 24 እያሉ ነው የሚናገሩት (energetic መሆናቸውን ለመግለፅ ይመስለኛል፤) እንዲያውም የ24 ዓመት ሰው እንዴት 33 ዓመት የሥራ ልምድ ይኖረዋል ሲባሉ÷ ቀሪው ‘over time’ የሰራሁት ነው ብለው መመለሳቸውን ነግረውናል፡፡ ለዚያ ነው እኔም አዳራሹ ውስጥ አንቺ ማለቴ፡፡ ስቀጥል፤

“ነገር ግን ከራስ ጋር ስለመወዳደር የተናገርሽውን ልስማማበት አልችልም፤ ምክንያቱም አንድ ሰው እየተራመደ እስከሆነ ድረስ ራሱን መቅደም ያቅተዋል ብዬ አልገምትም፡፡ ችግሩ ሰውዬው የሚራመደው በራሱ ፍጥነት መሆኑ ላይ ነው፡፡ በጥንችል ዘመን እኔ በኤሊ ፍጥነት ብጓዝ ምን ዋጋ አለው? ስለዚህ ከሰዎች ጋር መወዳደርን እንደ ጠላትነትነት ሳይሆን እንደኑሮ ፈሊጥ ልናየው ይገባል፤ ማደግ የምንችለው በትክክለኛው የውድድር pace መጓዝ ስንችል ብቻ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ ስለዚህ ይህንን ብታብራሪልኝ፡፡” ብዬ ደሰኮርኩ፡፡

ወ/ሮ ሙሉ ብዙም አልተቃወሙኝም፡፡ ከራስ ጋር መወዳደር ሲባል ተወዳዳሪ ዓለም እንዳለ መዘንጋት እንዳልሆነ አብራርተው፤ ስንወዳደር ግን በራሳችን መክሊት ልንወዳደራቸው ከሚገቡን ሰዎች ጋር መሆኑን አበክረው መከሩን፡፡ አለበለዚያ ዛሬ እኔ ተነስቼ ከኃይሌ ገ/ሥላሴ ጋር ካልሮጥኩ እና ካላሸነፍኩ ብል ዋጋ የለውም ማለታቸው እንደሆነ ነገሩን፡፡

ተስማማን፡፡ ይሄንን ጽሁፍ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ሐሳብ ግን የፈለቀው ይህንን ምልልስ በረዘዝኩበት (በገረብኩበት) በልምድ ማጋራቱ ዕለት ማግስት ነው፡፡ የራሴን ሐሳብ ራሴ ውድቅ አደረግኩት፡፡ ከሌሎች ጋር መወዳደር የሚለውን ወዲያ እናቆየውና እውን ብዙዎቻችን ከገዛ ራሳችን ጋር እየተወዳደርን ነውን?

ከራስ ጋር መወዳደር፤ ዘበት!
ጠዋት እነሳለሁ፣ እወጣለሁ፣ ሥራ እገባለሁ፣ ለምሳ እወጣለሁ፣ እመለሳለሁ፣ ከሥራ እወጣለሁ፣ ሰዎች አገኛለሁ፣ ወደቤት እመለሳለሁ፣ እተኛለሁ፡፡ ከዚያ የዚህ አንቀጽ መጀመሪያ ላይ ወዳለው መመለስ ነው፡፡ ብዙዎቻችን መንግሥት ወይም መስሪያ ቤታችን በየዓመቱ የሚጨምረውን ደሞዝ፣ ወይም አዲስ ሥራ ስንቀጠር የምናገኘውን ዕድገት ብቻ እየቆጠርን ካምናው ይሻላል፣ ከራሴ አንፃር ብዙ ተጉዣለሁ እንላለን፡፡ ግን ውሸት ነው፡፡ ከራሳችን ጋርም ሆነ ከሌሎች ጋር አልተወዳደርንም፡፡

ሁላችንም ፍራቻ አለብን፤ አዲስ ነገር የመፍራት፣ አዲስ ነገር የለመድኩትን ዋስትና ቢያሳጣኝስ እያሉ የመስጋት ‹ፎቢያ› አለብን፡፡ ስለዚህ ከለመድነው ትራክ አንወጣም፡፡ በዚያው ላይ ደጋግመን፣ ደጋግመን እንመላለስበታለን፡፡ ሕይወታችን ልክ በስታዲዬም ትራክ ላይ እንደሚደረግ ውድድር ነው፡፡ የመጀመሪያዎቹን አራትመቶ ሜትሮች ብቻ አዲስ ትራክ እየረገጥን እንሮጣለን፤ ከዚያ በኋላ ግን እየደግምነው፣ እየደግመነው እንሽከረከራለን፡፡ ስንጀምረው የነበረን ሞራል እና ጥንካሬ ደግሞ እየከዳን፣ እየከዳን ይመጣል፡፡ መጨረሻ ላይ አብረውን አንድ ትራክ ላይ ሲሮጡ ከነበሩ ሰዎች አንፃር ተመዝነን አሸናፊ እንባላለን፡፡

ባለፉበት መንገድ ደጋግሞ መመላለስ የብዙሐኑ ዕጣ ፈንታ ነው፡፡ ብዙሐኑ ሁሌም ቢሆን ቲፎዞ ነው፡፡ በሕይወት ዓለም ጥቂት ተጫዋቾች አሉ፡፡ ከተጫዋቾቹ ውስጥ የሚያሸንፉት ደግሞ የጥቂት ጥቂቶች ናቸው፡፡ ብዙሐኑ የሚደግፈው ቡድን ቢሸነፍም ባይሸነፍም በለመደው መንገድ እየቶፈዘ የሚያልፍ እዚህ ግባ የማይባል ነገር ግን ብዙ የሚል ቅጥያ ያለው ተመልካች ነው፡፡

የሚራመዱ ሰዎች በሕይወታቸው አዲስ ነገር መሞከር የማይፈሩ፤ እየሞከሩ፣ እየወደቁና እየተነሱ፣ እየቀየሩና እየተቀየሩ ባለፉበት መንገድ እንደታቦት ሳይመለሱ የሚጓዙ ናቸው፡፡

ዕድሜ በየዓመቱ በአንድ ይጨምራል፤ ደሞዝም እንደዚያው ሊጨምር ይችላል፡፡ በሕይወታችን የምናበረክተው ከገንዘብ በላይ ትርጉም ወይም መልክ ያለው ነገርስ በየዓመቱ ስንት ይጨምራል? በአምና ትራክ ላይ እየተሽከረከርን፣ አንድም እሴት ለማንጨምር ለኛ - ከአምናው ላልተሸልን ሰዎች - ወዮልን!!!

Comments

Popular posts from this blog

The "Corridor Development" is a Façade of the Prosperity Party

Befekadu Hailu I have seen a news report claiming that 40% of central Addis Ababa will be demolished for the corridor development; I am not able to confirm the validity of the news but it sounds real to me given the size of massive operations in the demolition of old neighborhoods and construction of bike lanes, green areas, and glittering street lights. I like to see some beauty added to my city but cannot help mourning the slow death of it too. Addis Ababa was already in a huge crisis of housing and the demolition of houses is exacerbating it. Apparently, Prime Minister Abiy Ahmed is eager to showcase his vision of prosperity by demonstrating how fast his administration can do magic by beautifying the front sides of the streets with lights, new pavements, and painted fences ("to fake it until he makes it" in my friend's words). Therefore, he and his party do not care about the miserable human stories behind the scenes and they will harass you if you tell it (Azeb Woku...

መጽሐፍ የሚወጣው፣ የተዋነይ ዘ ጎንጅ 5 መሥመር ቅኔ

ጎንጅ ቅኔ ያጠናበት ደብር ሥም ነው። ደብረ ጥበብ ጎንጅ ቅዱስ ቴዎድሮስ ገዳም። ተዋነይ የባለቅኔው ሥም ነው። (የግዕዝ ትርጉሙ "ዋናተኛ" ማለት ነው።) ሊቁ ተዋነይ የልኅቀቱን ያክል እምብዛም አይወራለትም፤ ነገር ግን በዘመኑ ወደር የሌለው ልኂቅ ስለመሆኑ ሥራው ይናገራል። የሕይወት ተፈራ "Mine to Win" የተሰኘ ድርሰት መቼቱን በዐፄ ዮሓንስ ንግሥና ዘመን፣ በጎጃም/ጎንደር የቅኔ መማሪያ ደብሮች ያደረገ ልብወለድ ነው። ልቦለዱ የቅኔ ትምህርት ስርዓትን ያስተዋውቀናል፤ በበኩሌ የቅኔ ትምህርትን እና የቅኔ ሊቃውንት ታላቅነት ቀድሞ ከነበረኝ ግንዛቤ የበለጠ እንዲሆን አድርጎኛል። በተለይ የተዋነይ ዘ ጎንጅ (በውኑ ዓለም የነበረ ባለቅኔ) ተከታይዋ አምስት መሥመር ቅኔ መጽሐፍ የሚወጣት እንደሆነች ልቦለዱ አሳሰበኝ። ወይም በአጭሩ ብዙ ምዕራባውያን ስንት መጽሐፍ የጻፉለት ፍልስፍናን በአምስት መሥመር ይዟል። የቅኔው ትርጓሜ የመጽሐፍ ቅዱስን እና የመጽሐፍ ቅዱሱን ፈጣሪ ኅልውና ይሞግታል። “የአምን ወይገኒ ኵሉ ዓለም በዘፈጠረ ለሊሁ ብዙኃን እንዘ ይገንዩ ይስግዱ ቅድሜሁ ለነጽሮ ዝኒ ነገር እሥራኤል ከመይፍርሑ ሙሴ ፈጠረ ፈጣሪሁ ወ ፈጣሪ ፈጠረ ኪያሁ።” (ተዋነይ ዘ ጎንጅ። ምንጭ፣ሕይወት ታደሰ ወደአማርኛ የተረጎመችው የሕይወት ተፈራ መጽሐፍ) ትርጉሙን በኋላ እመለስበታለሁ። ስለተዋነይ መጀመሪያ የሰማሁት የበውቀቱ መጽሐፍ ላይ ነበር። እሱም በጨረፍታ - “የሌሊት ዜማዎች” የሚለው ግጥሙ ውስጥ። በውቀቱ ተዋነይን በግጥሙ ግርጌ ማስታወሻው አስተዋውቆን ያልፋል፣ “ተዋነይ በቅኔ ቤት አፈ ታሪክ ሞትን በግዝት ለሰባት ዓመታት ያቆመ ጀግና ነው"። ከዚያ በኋላ፣ አዲስ አድማስ ላይ የወጣ አንድ ጽሑፍ ተዋነይ የተላከበትን ...

የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ

በፍቃዱ ዘ . ኃይሉ “የአዲስ አበባ ብሔርተኝነት” ቢኖር ኖሮ መሪው ልጅ ሚካኤል ይሆን ነበር። አሁን አሁን እሱ ስለ አዲስ አበባ የዘፈናቸውን ዘፈኖች ቁጥር ራሱ በትክክል መቁጠር ይቸግረኛል። ለአዲስ አበባ ከተዘፈኑ ዘፈኖቹ ውጪም በየዘፈኑ ውስጥ የሚጨማምራቸው መልዕክቶች በራሳቸው መወድሰ አዲስ አበባ ናቸው። ለምሳሌ፣ በቅርቡ በለቀቀው ‘አዲስ አራዳ’ በተሰኘው አልበሙ ውስጥ ‘የድሬ ልጅ’ የሚል ዘፈን አለው። ዘፈኑ የተዘጋጀው ያው የአዲስ አበባ እህት ተደርጋ የምትቆጠረውን ድሬ ዳዋን ለማወደስ ነበር። ልጅ ሚካኤል ግን የአዲስ አበባ ፍቅሩ ያመልጠውና የሚከተለውን ያቀነቅናል፦ “መጣልሽ በሏት፣ ድሬ ድረስ፣  ከአዱ ገነት፣ ከሸገር፣ ከአዲስ ደረሰ፣... የሸገር ልጅ አራዳ ነው፣ ሰው አክባሪ፣ ሰው ወዳዱ፣ ቀላጅና ተረበኛ፣ ፍቅር ይዞ የሚተኛ፣ ‘አለው’ የለ፣ ‘የለው’ የለ፣ ከሁሉ ጋ፣ ግባ ጀባ...፤” ፤ ልጅ ሚካኤል በዚህ አልበሙ ብቻ አዲስ አበባን የሚያውድሰባቸው ሌሎችም ዘፈኖች አሉ፤ ‘ አዲስ አራዳ ’ የሚለው የአልበሙ መጠሪያ እና ‘ሸገር’ የሚሉት ዘፈኖቹ ዋነኞቹ ናቸው። ታዲያ እንዲህ በአዲስ አበባ ፍቅር የሚቃጠለው ልጅ ሚካኤል "ሊነግረን የሚፈልገው ምንድን ነው?" የሚለው ጥያቄ ደጋግሞ ይመጣብኛል። ይህ የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ ምንነትን ለመረዳት የሚጥር ፖለቲካዊ መጣጥፍ ነው። ‘አዲሱ አራዳ’ ማነው? በዚህ ዘፈኑ በብዙዎቻችን ዕድሜ የትዝታ ማኅደር ውስጥ የሚገኙ ነገር ግን በአዲስ አበባ ልማት ሥም የፈረሱ እና እየተረሱ ያሉ ሰፈሮችን ሥም ያነሳሳል። ዘፈኑ በግጥሙም በዜማውም፣ የሐዘን እንጉርጉሮ ያለበት ነው። ምሳሌ እንውሰድ፦ “ጨርሰሽ ስትወጪ ከቡፌ ዳ’ላጋ፣ ጠብቂኝ እንዳልል፣ ቆመሽ መሐሙድ’ጋ፣ አገር ...