Skip to main content

የሐበሻ አምልኮ በኢትዮጵያ


(መግባቢያ፤ በዚህ ጽሁፍ ‘ሐበሻ’ ማለት ኢትዮጵያዊ፣ ‘አምልኮ’ ማለትም የተጋነነ አድንቆት የሚል ትርጉም ብቻ አላቸው፡፡) ‹የፈረረንጅ አምልኮበኢትዮጵያ› በሚል በጻፍኩት ጽሁፍ ተበሳጭተው÷ ጠንከር ያለ ነቀፌታቸውን ያደረሱኝ በርካቶች ናቸው፡፡ (በተለይም ethiopianreview.com ላይ!) የዚያን ቀጣይ ጽሁፍ በዚህ ርዕስ ለመጻፍ የተገደድኩት ያለፈው ጽሁፍ ስህተት መሆኑን አምኜ በተቃራኒው ለማረም ቢሆን ‹‹መልካም ነበር፡፡›› ግን አይደለም፤ ያም ሆነ ይህ ጽሁፍ ማሕበረሰባችንን መነቀፍ ባለበት ጉዳይ ለመንቀፍ የማይሳሱ ጽሁፎች ናቸው፡፡

በመጀመሪያ የቀደመው ጽሁፍ ለምን ነቃፊ በዛበት የሚል ጥያቄ ማንሳቱ ተገቢ መስሎ ይሰማኛል፡፡ የሁሉንም አስተያየት ሰጪዎች መልዕክት ያለምንም ማንገራገር በአንድ ጨፍልቆ መረዳት ይቻላል፡፡ ኢትዮጵያውያን ለባዕድ (ማለትም ለፈረንጅ) አምልኮ ወይም አድንቆ እጃቸውን የሰጡት ከመቼ ጀምሮ ነው በሚለው ጥያቄ ውስጥ እኔ መልስ ይሆናል ያልኩት ክርስትና ወደኢትዮጵያ መግባት ከጀመረ ወዲህ ነው የሚለውን ነው፡፡ ብዙዎች ክርስትና መነካቷን አይወዱምና የቁጣ ናዳ አወረዱብኝ ማለት ይቀላል፡፡ (ለጨዋታ ያህል ይሄ ጽሁፍ ‹‹ናዳን ለማቆም የተሮጠ ግለሰባዊ ሩጫ›› ነው ልንለው አንችላለን፡፡) እንዲያውም ክርስትና ለኢትዮጵያውያን የተሰፋ (ከባዕድ ያልወረስነው) እንደሆነ ሊያስረዱኝ የሞከሩ ሰዎችም አልጠፉም፡፡ ይሄ ሐሳብ ነው ወደዛሬው ጽሁፌ የሚያንደረድረኝ - የሐበሻ አምልኮ ብዬዋለሁ፡፡


በመጀመሪያ ማነው የመጀመሪያው?
በዕውቀቱ ስዩም ከአስቂኝ ወጎቹ መካከል በአንዱ÷ ኢትዮጵያውያን ያለቅጥ አንደኝነታችንን ማውራት እንደምንወድ አትቷል፡፡ ‹‹አሁን ለምሳሌ›› ብሎ ነገሩን በቀልድ ያጠናክረዋል፤ ‹‹እኔ በቤተሰቤ ውስጥ ሁለተኛ ልጅ በመሆን የመጀመሪያው ነኝ፡፡›› አይሁዶች ክርስትናን ሳይቀበሉት እኛ በመቀበላችን ወይም አረቦች እስልምናን ሳይቀበሉት እኛ በመቀበላችን÷ እኛ የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ወይም ሙስሊሞች ነን ብሎ መደምደም እኛን ማምለክ ነው፡፡ በሌላ በኩል እኛ ከሌሎቹ ቀድመን መቀበላችን (ወይም ተቀብለን መቅረታችን) ማሕበረሰባችን ለማመን ወይም የሌሎችን ተጽዕኖ በቀላሉ ለመቀበል የተፈጠረ እንዲመስል ያደርገዋል፡፡

በአርኪዮሎጂ ሉሲ አለች፣ በመጽሃፍ ቅዱስ የጊዮን ወንዝ (አባይ አለ፤ ‹‹ወንዝም ገነትን ያጠጣ ዘንድ ከኤደን ይወጣ ነበር…..የሁለተኛውም ወንዝ ስም ግዮን ነው፤ እርሱም የኢትዮጵያን ምድር ሁሉ ይከብባል።›› /ዘፍ. 2÷10-13/ እንዲል)፣ በታሪክም እንዲሁ እስከሦስት ሺኅ ዓመት ወደኋላ ተጉዘን ኢትዮጵያን ማግኘት እንችላለን፡፡ እንደኢትዮጵያዊ ዋንጫ ባያሸልምም ‹‹አንደኝነታችንን›› መዘከር ያስደስታል፡፡ ሌሎችም ሃገራት የራሳቸውን ‹‹አንደኝነት›› የሚዘክሩ ነገሮችን እንደሚያጣቅሱ ልብ ማለትም ያስፈልጋል፡፡ ስለዚህ ባሳለፍናቸው የኢትዮጵያ የታሪክ ዓመታት÷ ከወግና ከትዝታ በቀር ለዚህ ትውልድ የተረፈው ምንድር ነው? ከዚያም በላይ የሚያሳፍረው ደግሞ እኛስ ለመጪው ትውልድ ምንድር ነው የምናወርሰው የሚለው ነው? ሌላው ቀርቶ ሉሲን እንኳን ቆፍረው ያወጡልን ባዕዳን ናቸው፡፡ አሁንም የአክሱምን ስልጣኔ፣ የላሊበላን ምስጢር እየቆፈሩ የሚነግሩን እነርሱው ናቸው፡፡

የትኛው ኢንዱስትሪያችን ነው ትውፊታዊውን የሸክላ ሥራ እና የሽመና ጥበብ ወደዘመናዊነት ያሸጋገረው? የእጅ ጥበበኞችን ‹‹አንጥረኛ/ቡዳ/ሞረቴ/ባለእጅ›› የሚሉ ከደረጃ የሚያዋርዱ ስሞችን እየሰጠ እንዲከስሙ ያደረገው ማነው? ‹‹ካልለመኑ ይቆመጣሉ›› በሚል እየለመኑ ብቻ የሚተዳደሩ ማሕበረሰቦች ያሉባት አገር የማን ናት? ሥራ የማይነካባቸው ‹‹በዓላት›› እንደጉድ ያሏት ሃገር የማን ናት?

የሁሉም ሰው ምርጫ ሆነና÷ በታሪካችን የሚነገረውም ሆነ እንዲነገር የምንፈልገው በጎ፣ በጎውን ብቻ ነው፡፡ ዘወትር የምንዘክረው በዓለም ቀዳሚ የሚያሰኘንን እውነታ ብቻ ነው፡፡ ይምረር እንጂ ይሄም እውነታችን ነው፡፡ ሠራተኛ የሕብረተሰብ ክፍሎችን በማንኳሰስም የመጀመሪያዎቹ ነን፡፡

አሁን በዚህ ትውልድ ዘንድ ኢትዮጵያ በዚህ፣ በዚህ ቀዳሚ ነበረች የሚል ነገር ሳይሆን የሚያስፈልገን ‹‹ቀድማ ጀምራ ለምን ኋላ ቀረች?›› የሚል ነው፣ ‹‹መልሳ ለመቅደም ምን ታድርግ?›› ማለት ነው የሚያስፈልገን፡፡

የሚመለክ ‹‹ሐበሻ›› ለመፍጠር
የወደፊቷን ኢትዮጵያ ራዕይ አድርጎ ለሚጓዝ ሰው÷ መንገዱ ቀላል ነው፡፡ ኢትዮጵያውያንን ወደኋላ ያስቀረንን ኋላ ቀር የአሠራር ዘዴ እና የሥራ ባሕል ብሎም ሠራተኝነትን የማንቋሸሽ ልማድ ቀርፈነዋል ወይ ብሎ መጠየቅ የመጀመሪያው ርምጃ ነው፡፡ በማሕበረሰቡ ‹‹ዝቅተኛ›› በሚባሉ የሥራ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ሰዎችን የምናይበት ዓይን ከአባቶቻችን ይለያል?

የሐበሻ ቀሚስ ከቻይና ማስገባት ከመጀመራችን በፊት የሽመና ሥራን በዘመናዊ አሠራር የሚለውጡ ኢትዮጵያዊ መሃንዲሶች የታሉ? የሸክላ፣ የመሶብ እና እርቦ ሥራዎች ከየመቃብራቸው ተነስተው ማደግ ካልጀመሩ ሐበሻም የለ! ትንሳኤም የለ!

የዚህ ጽሁፍ ዓላማ ‹‹እኔ ምን ማድረግ እችላለሁ?›› ብሎ ጠያቂ እና ተግባሪን መቀስቀስ ነው፡፡ እኔ እንደመሃንዲስ ከአለፈው ታሪካችንና ከሕዝባችን ወቅታዊ ፍላጎት በመነሳት ምን መፈልሰፍ እችላለሁ? እኔ እንደሐኪም ከባሕላዊ ሕክምናዎች በመነሳት ምን ዓይነት ፈውስ አሊያም ግንዛቤ መፍጠር እችላለሁ? እኔ እንደፖለቲከኛ ምን ዓይነት ለውጥ ማምጣት እችላለሁ? እኔ እንደጸሃፊ አመለካከትን በመቀየር፣ መረጃ በመስጠት እና ወዘተርፈ ምን ማድረግ እችላለሁ? እኔ ምን ማድረግ እችላለሁ በማለት - ብዙ ነገር ማድረግ እንችላለን!!!

Comments

Popular posts from this blog

The "Corridor Development" is a Façade of the Prosperity Party

Befekadu Hailu I have seen a news report claiming that 40% of central Addis Ababa will be demolished for the corridor development; I am not able to confirm the validity of the news but it sounds real to me given the size of massive operations in the demolition of old neighborhoods and construction of bike lanes, green areas, and glittering street lights. I like to see some beauty added to my city but cannot help mourning the slow death of it too. Addis Ababa was already in a huge crisis of housing and the demolition of houses is exacerbating it. Apparently, Prime Minister Abiy Ahmed is eager to showcase his vision of prosperity by demonstrating how fast his administration can do magic by beautifying the front sides of the streets with lights, new pavements, and painted fences ("to fake it until he makes it" in my friend's words). Therefore, he and his party do not care about the miserable human stories behind the scenes and they will harass you if you tell it (Azeb Woku...

የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ

በፍቃዱ ዘ . ኃይሉ “የአዲስ አበባ ብሔርተኝነት” ቢኖር ኖሮ መሪው ልጅ ሚካኤል ይሆን ነበር። አሁን አሁን እሱ ስለ አዲስ አበባ የዘፈናቸውን ዘፈኖች ቁጥር ራሱ በትክክል መቁጠር ይቸግረኛል። ለአዲስ አበባ ከተዘፈኑ ዘፈኖቹ ውጪም በየዘፈኑ ውስጥ የሚጨማምራቸው መልዕክቶች በራሳቸው መወድሰ አዲስ አበባ ናቸው። ለምሳሌ፣ በቅርቡ በለቀቀው ‘አዲስ አራዳ’ በተሰኘው አልበሙ ውስጥ ‘የድሬ ልጅ’ የሚል ዘፈን አለው። ዘፈኑ የተዘጋጀው ያው የአዲስ አበባ እህት ተደርጋ የምትቆጠረውን ድሬ ዳዋን ለማወደስ ነበር። ልጅ ሚካኤል ግን የአዲስ አበባ ፍቅሩ ያመልጠውና የሚከተለውን ያቀነቅናል፦ “መጣልሽ በሏት፣ ድሬ ድረስ፣  ከአዱ ገነት፣ ከሸገር፣ ከአዲስ ደረሰ፣... የሸገር ልጅ አራዳ ነው፣ ሰው አክባሪ፣ ሰው ወዳዱ፣ ቀላጅና ተረበኛ፣ ፍቅር ይዞ የሚተኛ፣ ‘አለው’ የለ፣ ‘የለው’ የለ፣ ከሁሉ ጋ፣ ግባ ጀባ...፤” ፤ ልጅ ሚካኤል በዚህ አልበሙ ብቻ አዲስ አበባን የሚያውድሰባቸው ሌሎችም ዘፈኖች አሉ፤ ‘ አዲስ አራዳ ’ የሚለው የአልበሙ መጠሪያ እና ‘ሸገር’ የሚሉት ዘፈኖቹ ዋነኞቹ ናቸው። ታዲያ እንዲህ በአዲስ አበባ ፍቅር የሚቃጠለው ልጅ ሚካኤል "ሊነግረን የሚፈልገው ምንድን ነው?" የሚለው ጥያቄ ደጋግሞ ይመጣብኛል። ይህ የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ ምንነትን ለመረዳት የሚጥር ፖለቲካዊ መጣጥፍ ነው። ‘አዲሱ አራዳ’ ማነው? በዚህ ዘፈኑ በብዙዎቻችን ዕድሜ የትዝታ ማኅደር ውስጥ የሚገኙ ነገር ግን በአዲስ አበባ ልማት ሥም የፈረሱ እና እየተረሱ ያሉ ሰፈሮችን ሥም ያነሳሳል። ዘፈኑ በግጥሙም በዜማውም፣ የሐዘን እንጉርጉሮ ያለበት ነው። ምሳሌ እንውሰድ፦ “ጨርሰሽ ስትወጪ ከቡፌ ዳ’ላጋ፣ ጠብቂኝ እንዳልል፣ ቆመሽ መሐሙድ’ጋ፣ አገር ...

መጽሐፍ የሚወጣው፣ የተዋነይ ዘ ጎንጅ 5 መሥመር ቅኔ

ጎንጅ ቅኔ ያጠናበት ደብር ሥም ነው። ደብረ ጥበብ ጎንጅ ቅዱስ ቴዎድሮስ ገዳም። ተዋነይ የባለቅኔው ሥም ነው። (የግዕዝ ትርጉሙ "ዋናተኛ" ማለት ነው።) ሊቁ ተዋነይ የልኅቀቱን ያክል እምብዛም አይወራለትም፤ ነገር ግን በዘመኑ ወደር የሌለው ልኂቅ ስለመሆኑ ሥራው ይናገራል። የሕይወት ተፈራ "Mine to Win" የተሰኘ ድርሰት መቼቱን በዐፄ ዮሓንስ ንግሥና ዘመን፣ በጎጃም/ጎንደር የቅኔ መማሪያ ደብሮች ያደረገ ልብወለድ ነው። ልቦለዱ የቅኔ ትምህርት ስርዓትን ያስተዋውቀናል፤ በበኩሌ የቅኔ ትምህርትን እና የቅኔ ሊቃውንት ታላቅነት ቀድሞ ከነበረኝ ግንዛቤ የበለጠ እንዲሆን አድርጎኛል። በተለይ የተዋነይ ዘ ጎንጅ (በውኑ ዓለም የነበረ ባለቅኔ) ተከታይዋ አምስት መሥመር ቅኔ መጽሐፍ የሚወጣት እንደሆነች ልቦለዱ አሳሰበኝ። ወይም በአጭሩ ብዙ ምዕራባውያን ስንት መጽሐፍ የጻፉለት ፍልስፍናን በአምስት መሥመር ይዟል። የቅኔው ትርጓሜ የመጽሐፍ ቅዱስን እና የመጽሐፍ ቅዱሱን ፈጣሪ ኅልውና ይሞግታል። “የአምን ወይገኒ ኵሉ ዓለም በዘፈጠረ ለሊሁ ብዙኃን እንዘ ይገንዩ ይስግዱ ቅድሜሁ ለነጽሮ ዝኒ ነገር እሥራኤል ከመይፍርሑ ሙሴ ፈጠረ ፈጣሪሁ ወ ፈጣሪ ፈጠረ ኪያሁ።” (ተዋነይ ዘ ጎንጅ። ምንጭ፣ሕይወት ታደሰ ወደአማርኛ የተረጎመችው የሕይወት ተፈራ መጽሐፍ) ትርጉሙን በኋላ እመለስበታለሁ። ስለተዋነይ መጀመሪያ የሰማሁት የበውቀቱ መጽሐፍ ላይ ነበር። እሱም በጨረፍታ - “የሌሊት ዜማዎች” የሚለው ግጥሙ ውስጥ። በውቀቱ ተዋነይን በግጥሙ ግርጌ ማስታወሻው አስተዋውቆን ያልፋል፣ “ተዋነይ በቅኔ ቤት አፈ ታሪክ ሞትን በግዝት ለሰባት ዓመታት ያቆመ ጀግና ነው"። ከዚያ በኋላ፣ አዲስ አድማስ ላይ የወጣ አንድ ጽሑፍ ተዋነይ የተላከበትን ...