Skip to main content

ዴሞክራሲ ኢትዮጵያ ውስጥ አለ ወይስ የለም? (እርስዎ ምን ይላሉ?)


ዴሞክራሲ ትልቅ ፅንሰ ሐሳብ ነው፡፡ ከዚያም ባሻገር ሆኖም ልክ እንደአብዛኛዎቹ የዓለማችን እውነታዎች ፍፁም ሊሟላ አይችልም፡፡ ነገር ግን ምሁራን ዴሞክራሲን መለኪያ ቅንጣቶችን ያስቀምጡለታል፡፡ በነዚህ ቅንጣቶች እየለኩም ነው ሃገራትን ዴሞክራሲያዊ፣ ከፊል ዴሞክራሲያዊ፣ ፀረ ዴሞክራሲያዊ… እያሉ ሲፈርጁ የምንመለከተው፡፡ እኛስ፣ ኢትዮጵያውያን ራሳችን ዴሞክራሲያችንን መመዘን ብንችል ብላችሁ ተመኝታችሁ አታውቁም፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ ጥቂት የማሰቢያ ቋቶች (think tanks) አሁን አሁን ብቅ ብቅ ማለት ቢጀምሩም ብዙዎቹ ደፍረው ፖለቲካዊ ጥያቄዎችን እያነሱ ጥናት አያደርጉም፡፡  በየዓመቱም እየገመገሙ ‹‹አድገናል፣ ወድቀናል›› አይሉንም፡፡ አገራችን ‹‹በማደግ ላይ ያለች›› በመሆኗ እና ምናልባትም እጅግ ዴሞክራሲያዊ የሆኑ መንግስታት ስታገኝ እንዲህ ዓይነት ተቋማት ወደፊት እየተበራከቱ እንደሚመጡ ተስፋ ማድረግ ብንችልም እስከዚያው ግን እኛ የበኩላችንን ጥረት ብናደርግስ?

ብዙ ጊዜ የሚሞግተኝ ጥያቄ አለ፡፡ (በተለይ ይህንን ጦማር ለማንበብ የታደልነው) ብዙዎቻችን ከተሜዎች ወይም ከተማ ቀመስ ነን፡፡ 80 በመቶ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን የገጠር ነዋሪዎች ናቸው፤ በይነመረብ (Internet) ለነርሱ ቅንጦት ነው፡፡ ለብርሃን ያህል የኤሌክትሪክ ኃይል እንኳን ለማግኘት አልታደሉምና ማለቴ ነው፡፡ ታዲያ ስለኢትዮጵያ ስናወራ ከራሳችን ስሜት እና ልምድ ተነስተን እንደመሆኑ የብዙሐኑን ስሜት እና እውነት ማንፀባረቃችንን እርግጠኛ መሆን ይቸግረኛል፡፡ እርግጥ ነው፤ ገጠሬው ኢትዮጵያዊ የሚባልለትን ያህል እንዳልበለፀገ እግር ጥሎን ስንሄድ፣ ዘመድ አዝማዶቻችን ሲመጡ እና በሌሎችም አቋራጮች እንገነዘባለን፡፡

ችግሩ
ገጠሬው ኢትዮጵያዊ ለበይነመረብ ብቻ ሳይሆን ለቀለም ትምህርት እና መረጃም ሩቅ ነው፡፡ (ይህ ጥቂት የማይባሉ ከተሜዎችን ያልለቀቀ ነገር ቢሆንም፤) ገጠሬው ግን እስካሁን ‹‹ንጉሥ አይከሰስ›› በሚለው እምነቱ እንደፀና ነው፡፡ የዴሞክራሲ ፅንሰ ሐሳብ እና ፍላጎቱ ዘልቆ ገብቶታል ለማለት የሚያስደፍር እውነት አይታየኝም፡፡

እንዲህ ዓይነቱ እውነት በየትኛውም ዓለም የፀና ነው፡፡ ዕጣ ፈንታ ከውልደታቸው እስከ ዕድገታቸው ነገሮችን የማወቅ ዕድል ያመቻችላቸው ሰዎች አሉ፤ እነዚህ ሰዎች ደግሞ ተፈጥሮ ያመቻቸላቸውን የመልካም አጋጣሚ ብድር መመለስ አለባቸው ብዬ አምናለሁ፡፡ ተጠቃሚ ዜጎች፣ ጥቅም ለጎደለባቸው መታገል አለባቸው ነው ነገሬ፡፡ ስለዚህ ገጠሬው ያፈራውን እህል ብቻውን እንደማይበላው ሁሉ ከተሜውም ስለዴሞክራሲ ገብቶኛል የሚል ከሆነ የዴሞክራሲን አጀንዳ ጠረጴዛ ላይ ሲያስቀምጥ ለከተሜው ብቻ ሳይሆን ለገጠሬውም ጭምር ነው ማለት ነው፡፡

ከላይ ለመጥቀስ እንደሞከርኩት ገጠሬው ስለዴሞክራሲ የሚኖረው ግንዛቤ ከከተሜው ያነሰ ነው የሚል መስማሚያ ላይ መድረስ አወዛጋቢ አይመስለኝም፡፡ እስኪ ደግሞ ኢትዮጵያዊው ከተሜ በአሁኑ ስርዓት ስለሚተገበረው ዴሞክራሲ ምን ይላል የሚል ጉጉት አደረብኝ፡፡ ነገር ግን ከተሜውን ሁሉ ማግኘት አይቻልም፡፡ ስለዚህ የነበረኝ አማራጭ ለበይነመረብ ተጠቃሚ ኢትዮጵያዊያን (ናሙና ከተሜዎች መሆናቸው አያጠራጥርም፤ ነገር ግን ከተሜ ሁሉ በይነመረብ ተጠቃሚ አይደለም፡፡ ቢሆንም በይነመረብ ተጠቃሚዎች ለዓለማዊ መረጃዎች ቅርብ እንደመሆናቸው ስለዴሞክራሲም የሚኖራቸው ግንዛቤ የተሻለ እንደሚሆን በማመን) የመስመር ላይ ቅኝት (online survey) አዘጋጅቼ ውጤቱን ለመተንተን እና በጦማሬ ላይ ለማተም ፈለግኩ፡፡ እነሆ ጥያቄዎቹንም አዘጋጅቼ እዚህ አቀረብኩላችሁ፡፡

መጠይቁን ሳዘጋጅ የተጠቀምኩት በርካታ ምሁራን ዴሞክራሲ ይለካባቸዋል ብለው በሚያስቀምጧቸው ቅንጣቶች ነው፡፡ እነዚህም ፍትሐዊ ምርጫ፣ ነፃ ሲቪክ ማሕበረሰብ፣ በነፃ ሐሳብን የመግለፅ መብት፣ የሕግ የበላይነት፣ የብዙሐን መሪነት፣ የግለሰብ ነፃነት እና ሌሎችንም ያካትታሉ፡፡  

ጥያቄዎቹን ከማቅረቤ በርካቶች መሙላት መጀመራቸውን ሪፖርቱ ላይ ተመልክቻለሁ፡፡ አንዳንድ አስተያየቶች እየደረሱኝም ነው፡፡ ጥያቄዎቹ ‹አማካይ› የላቸውም (ጥቁር እና ነጭ ብቻ ናቸው)፣ የተፈለገውን ያህል ብዛት ያለው ሰው ምላሽ መስጠት ሊፈራ ይችላል፣ የዚህ ቃለ መጠይቅ ድምዳሜ ምን ሊሆን እንደሚችል የሚገነዘቡ የ'አሁኑ'ስርዓት ተጠቃሚ ነን ባዮች ሊፈጥሩት የሚችሉትን ድምዳሜ የማስቀየር ተፅዕኖ የሚሉት ጥቂቶቹ ናቸው፡፡

ስጋቶቹ እና እንደድክመት የተነሱት እና ሊነሱ የሚችሉት ሐሳቦች ተገቢም ትክክልም ናቸው፡፡ ሆኖም የዚህ አነስተኛ ቅኝት ዋና ዓላማ ከድምዳሜውም በላይ ነው፡፡ ስለዴሞክራሲያችን መወያየት መቻል፡፡ ስለዚህ ከላይ ጥያቄዎቹን በመሙላት በበይነመረብ ላይ ያለው የኢትዮጵያ ማሕበረሰብ ስለዴሞክራሲያችን ያለውን አመለካከት ጠቅላላ ምስል ለመገመት ይረዳን ዘንድ መጠይቁን በመሙላት የቻልነውን ያክል እንሞክር፡፡

Comments

Popular posts from this blog

The "Corridor Development" is a Façade of the Prosperity Party

Befekadu Hailu I have seen a news report claiming that 40% of central Addis Ababa will be demolished for the corridor development; I am not able to confirm the validity of the news but it sounds real to me given the size of massive operations in the demolition of old neighborhoods and construction of bike lanes, green areas, and glittering street lights. I like to see some beauty added to my city but cannot help mourning the slow death of it too. Addis Ababa was already in a huge crisis of housing and the demolition of houses is exacerbating it. Apparently, Prime Minister Abiy Ahmed is eager to showcase his vision of prosperity by demonstrating how fast his administration can do magic by beautifying the front sides of the streets with lights, new pavements, and painted fences ("to fake it until he makes it" in my friend's words). Therefore, he and his party do not care about the miserable human stories behind the scenes and they will harass you if you tell it (Azeb Woku...

መጽሐፍ የሚወጣው፣ የተዋነይ ዘ ጎንጅ 5 መሥመር ቅኔ

ጎንጅ ቅኔ ያጠናበት ደብር ሥም ነው። ደብረ ጥበብ ጎንጅ ቅዱስ ቴዎድሮስ ገዳም። ተዋነይ የባለቅኔው ሥም ነው። (የግዕዝ ትርጉሙ "ዋናተኛ" ማለት ነው።) ሊቁ ተዋነይ የልኅቀቱን ያክል እምብዛም አይወራለትም፤ ነገር ግን በዘመኑ ወደር የሌለው ልኂቅ ስለመሆኑ ሥራው ይናገራል። የሕይወት ተፈራ "Mine to Win" የተሰኘ ድርሰት መቼቱን በዐፄ ዮሓንስ ንግሥና ዘመን፣ በጎጃም/ጎንደር የቅኔ መማሪያ ደብሮች ያደረገ ልብወለድ ነው። ልቦለዱ የቅኔ ትምህርት ስርዓትን ያስተዋውቀናል፤ በበኩሌ የቅኔ ትምህርትን እና የቅኔ ሊቃውንት ታላቅነት ቀድሞ ከነበረኝ ግንዛቤ የበለጠ እንዲሆን አድርጎኛል። በተለይ የተዋነይ ዘ ጎንጅ (በውኑ ዓለም የነበረ ባለቅኔ) ተከታይዋ አምስት መሥመር ቅኔ መጽሐፍ የሚወጣት እንደሆነች ልቦለዱ አሳሰበኝ። ወይም በአጭሩ ብዙ ምዕራባውያን ስንት መጽሐፍ የጻፉለት ፍልስፍናን በአምስት መሥመር ይዟል። የቅኔው ትርጓሜ የመጽሐፍ ቅዱስን እና የመጽሐፍ ቅዱሱን ፈጣሪ ኅልውና ይሞግታል። “የአምን ወይገኒ ኵሉ ዓለም በዘፈጠረ ለሊሁ ብዙኃን እንዘ ይገንዩ ይስግዱ ቅድሜሁ ለነጽሮ ዝኒ ነገር እሥራኤል ከመይፍርሑ ሙሴ ፈጠረ ፈጣሪሁ ወ ፈጣሪ ፈጠረ ኪያሁ።” (ተዋነይ ዘ ጎንጅ። ምንጭ፣ሕይወት ታደሰ ወደአማርኛ የተረጎመችው የሕይወት ተፈራ መጽሐፍ) ትርጉሙን በኋላ እመለስበታለሁ። ስለተዋነይ መጀመሪያ የሰማሁት የበውቀቱ መጽሐፍ ላይ ነበር። እሱም በጨረፍታ - “የሌሊት ዜማዎች” የሚለው ግጥሙ ውስጥ። በውቀቱ ተዋነይን በግጥሙ ግርጌ ማስታወሻው አስተዋውቆን ያልፋል፣ “ተዋነይ በቅኔ ቤት አፈ ታሪክ ሞትን በግዝት ለሰባት ዓመታት ያቆመ ጀግና ነው"። ከዚያ በኋላ፣ አዲስ አድማስ ላይ የወጣ አንድ ጽሑፍ ተዋነይ የተላከበትን ...

የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ

በፍቃዱ ዘ . ኃይሉ “የአዲስ አበባ ብሔርተኝነት” ቢኖር ኖሮ መሪው ልጅ ሚካኤል ይሆን ነበር። አሁን አሁን እሱ ስለ አዲስ አበባ የዘፈናቸውን ዘፈኖች ቁጥር ራሱ በትክክል መቁጠር ይቸግረኛል። ለአዲስ አበባ ከተዘፈኑ ዘፈኖቹ ውጪም በየዘፈኑ ውስጥ የሚጨማምራቸው መልዕክቶች በራሳቸው መወድሰ አዲስ አበባ ናቸው። ለምሳሌ፣ በቅርቡ በለቀቀው ‘አዲስ አራዳ’ በተሰኘው አልበሙ ውስጥ ‘የድሬ ልጅ’ የሚል ዘፈን አለው። ዘፈኑ የተዘጋጀው ያው የአዲስ አበባ እህት ተደርጋ የምትቆጠረውን ድሬ ዳዋን ለማወደስ ነበር። ልጅ ሚካኤል ግን የአዲስ አበባ ፍቅሩ ያመልጠውና የሚከተለውን ያቀነቅናል፦ “መጣልሽ በሏት፣ ድሬ ድረስ፣  ከአዱ ገነት፣ ከሸገር፣ ከአዲስ ደረሰ፣... የሸገር ልጅ አራዳ ነው፣ ሰው አክባሪ፣ ሰው ወዳዱ፣ ቀላጅና ተረበኛ፣ ፍቅር ይዞ የሚተኛ፣ ‘አለው’ የለ፣ ‘የለው’ የለ፣ ከሁሉ ጋ፣ ግባ ጀባ...፤” ፤ ልጅ ሚካኤል በዚህ አልበሙ ብቻ አዲስ አበባን የሚያውድሰባቸው ሌሎችም ዘፈኖች አሉ፤ ‘ አዲስ አራዳ ’ የሚለው የአልበሙ መጠሪያ እና ‘ሸገር’ የሚሉት ዘፈኖቹ ዋነኞቹ ናቸው። ታዲያ እንዲህ በአዲስ አበባ ፍቅር የሚቃጠለው ልጅ ሚካኤል "ሊነግረን የሚፈልገው ምንድን ነው?" የሚለው ጥያቄ ደጋግሞ ይመጣብኛል። ይህ የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ ምንነትን ለመረዳት የሚጥር ፖለቲካዊ መጣጥፍ ነው። ‘አዲሱ አራዳ’ ማነው? በዚህ ዘፈኑ በብዙዎቻችን ዕድሜ የትዝታ ማኅደር ውስጥ የሚገኙ ነገር ግን በአዲስ አበባ ልማት ሥም የፈረሱ እና እየተረሱ ያሉ ሰፈሮችን ሥም ያነሳሳል። ዘፈኑ በግጥሙም በዜማውም፣ የሐዘን እንጉርጉሮ ያለበት ነው። ምሳሌ እንውሰድ፦ “ጨርሰሽ ስትወጪ ከቡፌ ዳ’ላጋ፣ ጠብቂኝ እንዳልል፣ ቆመሽ መሐሙድ’ጋ፣ አገር ...