Skip to main content

Hookah እና አሜሪካ


ይህንን ጽሁፍ ለመጻፍ ስነሳ ‹‹የኛ ሰው በአሜሪካ›› የሚል ርዕስ ልሰጠው ፈልጌ ነበር፡፡ ችግሩ ይሄ ርዕስ አሜሪካንን ረግጠው በተመለሱ ሰዎች ስለተለመደ ባይተዋርነት ተስማምቶኝ ተውኩት፤ በሌላ በኩል የየኛ ሰው በአሜሪካ ኑሮ በሁካ ብቻ አይገለፅም የሚል ርህራሄም ተሰምቶኛል፡፡

ሁካ - የሺሻ አሜሪካዊ ስሟ ነው፡፡ አዲስ ጋይድ የምትባል፣ በቀለም የተንቆጠቆጠች፣ ዲዛይኗ እና ጠረኗ ያማረ፣ ጽሁፎቿ ዋዘኛ፣ ዳያስፖራውን ኢላማ ያደረገች መጽሄት በአጋጣሚ እጄ ገብታ ሳገለባብጣት ማስታወቂያ እንደሚበዛባት አስተውያለሁ፡፡

ካየሁዋቸው ማስታወቂያዎች ውስጥ - በተለይም የአበሻ ካፌና ሬስቶራንቶቹ ማስታወቂያዎች ከዘጠኙ ስምንቱ ሁካን በስዕል ወይም በጽሁፍ አስተዋውቀዋል፡፡

የሁካ ማጨሻዋ እቃ በወርቃማ ቀለም የተንቆጠቆጠ፣ ዙሪያው በአረቢያል መጅሪስ የደመቀ፣ አፋቸው ላይ ጡሩምባ መሳይ የሁካውን ጫፍ የሰኩ ወይም እንደፈላ ጀበና ከአፋቸው ጢስ ቡልቅ፣ ቡልቅ የሚያደርጉ ሴቶች፣ ወዘተ፣ ወዘተ ለቁርስ ቤቶቹ ማስታወቂያ ሳይቀር ፍጆታ ሁነዋል፡፡

‹‹የኛ ሰዎች በአሜሪካ›› ታሰቡኝ!
ዘመድ ጥየቃ፣ ወይም ሚስት/ባል ፍለጋ፣ ወይም የቆጠቡትን አጥፍተው ለመመለስ የሚሄዱ ዳያስፖራዎች ‹‹የለመለመ ጫት ናፍቆኛል!›› የሚሏት ነገር ትዝ አለችኝ፡፡ የአገራችን ሰው ጫት መቃምን ዘመነኝነት ካደረገው ሰነባብቷል፡፡ ለጫት ግድ የለውም የሚባለው ሰው እንኳን ቅዳሜ እና እሁድን ማሳለፊያው ጫት ነው፡፡ እንዲያውም ‹‹ትልልቆቹ››፣ በየሳምነቱ የሥራ ቀናት ‹‹ቢዚ›› የሆኑት ሰዎች እሁድ እሁድ ‹‹ዛፍ ላይ እንውጣ›› እየተባባሉ ነው የሚጠራሩት፡፡ (ባለፈው ሰሞን የኛ ፕሬስ የተባለ ጋዜጣ ‹‹አርቲስቱ ከጓደኞቹ ጋር ጫት ለመቃም በየቀኑ አንድሺህ ብር ያወጣል›› ብሎ ያወራት ወሬ ስንት ፍልስምና አፈላስማኛለች መሰላችሁ? ስንት ሰው በአንድ ሺህ ብር በወር ስንት ቤተሰብ ለማስተዳደር አስማት በሚሰራባት አገር ውስጥ ‹‹አርቲስቱ›› በቀን አንድ ሺህ ብር ለጫት - ‹አጀብ!› አያሰኝም?)

የእንጦጦ ጎዳናዎች ዳርቻ ላይ ተኮልኩለው የሚቆሙ መኪኖች - ውስጣቸው ዙርባ ጫት ዙሪያ የሰፈሩ ባለጠጎች አሉባቸው፡፡ ፒያሣ ከማሕሙድ ሙዚቃ ቤት ወደ ሰይጣን ቤት ቁልቁል ባንኮ ዲሮማ ተደግፈው ሲወርዱ የሚያገኟቸው መኪኖችም የሚቆሙት ይህንኑ ጉዳይ ለማስፈጸም ነው፡፡ ሌላም፣ ሌላም ቦታ! በጫት ምርቃና የተጻፉ ፖለቲካዊ ትንታኔዎች በየጋዜጦቹ፣ በጫት ምርቃና የሚቀርቡ ፕሮግራሞች በየኤፍ ኤም ሬዲዮዎቹ፣ በጫት ምርቃና የሚወጡ ፖለሲዎች በየቤተመንግስቱ (ይቅርታ በቤተ መንግስቱ)፣ በጫት ምርቃና….?

ቢሆንም ግን ይሄ የአገርቤት አመል ውቅያኖስ ያቋርጣል የሚል ግምት አልነበረኝም፡፡ ነገር ግን እውነታው የእኛ ሰው - አገር አቋርጦ ሲሄድ ለሱሳሱስ ዕውቅና ከመስጠት የተሻገረ ስልጣኔ እንደማያገባው - ሬስቶራንቶችን በምግብ ምስል ከማስተዋወቅ ይልቅ - በሁካ ማጨሻ ጋን ማስተዋወቅ - እንደማሕበረሰብ ዋጋ የምንሰጠውን ነገር ግን እያስታወሰ የሚያስተዛዝበን ነገር ነው፡፡

እኔ እዚህ ቁጭ ብዬ ሳስበው በቅድሚያ የሚያቃጭልብኝ የዳያስፖራ ፖለቲካ ነው፡፡ በአገርቤት ያሉ አርቲስቶች በምርቃ የሚጽፉት ድርሰት እና ፊልም - መጀመሪያ ላይ ዋና ገጸ ባሕሪው የሚጠራበት ስም ተረስቶ መጨረሻ ላይ ሌላ ሲሆን ገጥሞኝ ያውቃል፡፡ አሁንም በሁካ ቤት ምክር የተመሰረቱ የዳያስፖራ ፓርቲዎች አገራችንን…… (እናንተ ጨርሱልኝ!)

---
ይሄ ጽሁፍ ከደሙ ነፃ የሆኑ ዳያስፖራዎችን አይመለከትም፡፡

Comments

  1. ...በሁካ ፖሊሲ ያውኳታል፡፡ ብዬ ጨረስኩልህ ፡)
    naodlive

    ReplyDelete

Post a Comment

Popular posts from this blog

The "Corridor Development" is a Façade of the Prosperity Party

Befekadu Hailu I have seen a news report claiming that 40% of central Addis Ababa will be demolished for the corridor development; I am not able to confirm the validity of the news but it sounds real to me given the size of massive operations in the demolition of old neighborhoods and construction of bike lanes, green areas, and glittering street lights. I like to see some beauty added to my city but cannot help mourning the slow death of it too. Addis Ababa was already in a huge crisis of housing and the demolition of houses is exacerbating it. Apparently, Prime Minister Abiy Ahmed is eager to showcase his vision of prosperity by demonstrating how fast his administration can do magic by beautifying the front sides of the streets with lights, new pavements, and painted fences ("to fake it until he makes it" in my friend's words). Therefore, he and his party do not care about the miserable human stories behind the scenes and they will harass you if you tell it (Azeb Woku...

የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ

በፍቃዱ ዘ . ኃይሉ “የአዲስ አበባ ብሔርተኝነት” ቢኖር ኖሮ መሪው ልጅ ሚካኤል ይሆን ነበር። አሁን አሁን እሱ ስለ አዲስ አበባ የዘፈናቸውን ዘፈኖች ቁጥር ራሱ በትክክል መቁጠር ይቸግረኛል። ለአዲስ አበባ ከተዘፈኑ ዘፈኖቹ ውጪም በየዘፈኑ ውስጥ የሚጨማምራቸው መልዕክቶች በራሳቸው መወድሰ አዲስ አበባ ናቸው። ለምሳሌ፣ በቅርቡ በለቀቀው ‘አዲስ አራዳ’ በተሰኘው አልበሙ ውስጥ ‘የድሬ ልጅ’ የሚል ዘፈን አለው። ዘፈኑ የተዘጋጀው ያው የአዲስ አበባ እህት ተደርጋ የምትቆጠረውን ድሬ ዳዋን ለማወደስ ነበር። ልጅ ሚካኤል ግን የአዲስ አበባ ፍቅሩ ያመልጠውና የሚከተለውን ያቀነቅናል፦ “መጣልሽ በሏት፣ ድሬ ድረስ፣  ከአዱ ገነት፣ ከሸገር፣ ከአዲስ ደረሰ፣... የሸገር ልጅ አራዳ ነው፣ ሰው አክባሪ፣ ሰው ወዳዱ፣ ቀላጅና ተረበኛ፣ ፍቅር ይዞ የሚተኛ፣ ‘አለው’ የለ፣ ‘የለው’ የለ፣ ከሁሉ ጋ፣ ግባ ጀባ...፤” ፤ ልጅ ሚካኤል በዚህ አልበሙ ብቻ አዲስ አበባን የሚያውድሰባቸው ሌሎችም ዘፈኖች አሉ፤ ‘ አዲስ አራዳ ’ የሚለው የአልበሙ መጠሪያ እና ‘ሸገር’ የሚሉት ዘፈኖቹ ዋነኞቹ ናቸው። ታዲያ እንዲህ በአዲስ አበባ ፍቅር የሚቃጠለው ልጅ ሚካኤል "ሊነግረን የሚፈልገው ምንድን ነው?" የሚለው ጥያቄ ደጋግሞ ይመጣብኛል። ይህ የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ ምንነትን ለመረዳት የሚጥር ፖለቲካዊ መጣጥፍ ነው። ‘አዲሱ አራዳ’ ማነው? በዚህ ዘፈኑ በብዙዎቻችን ዕድሜ የትዝታ ማኅደር ውስጥ የሚገኙ ነገር ግን በአዲስ አበባ ልማት ሥም የፈረሱ እና እየተረሱ ያሉ ሰፈሮችን ሥም ያነሳሳል። ዘፈኑ በግጥሙም በዜማውም፣ የሐዘን እንጉርጉሮ ያለበት ነው። ምሳሌ እንውሰድ፦ “ጨርሰሽ ስትወጪ ከቡፌ ዳ’ላጋ፣ ጠብቂኝ እንዳልል፣ ቆመሽ መሐሙድ’ጋ፣ አገር ...

መጽሐፍ የሚወጣው፣ የተዋነይ ዘ ጎንጅ 5 መሥመር ቅኔ

ጎንጅ ቅኔ ያጠናበት ደብር ሥም ነው። ደብረ ጥበብ ጎንጅ ቅዱስ ቴዎድሮስ ገዳም። ተዋነይ የባለቅኔው ሥም ነው። (የግዕዝ ትርጉሙ "ዋናተኛ" ማለት ነው።) ሊቁ ተዋነይ የልኅቀቱን ያክል እምብዛም አይወራለትም፤ ነገር ግን በዘመኑ ወደር የሌለው ልኂቅ ስለመሆኑ ሥራው ይናገራል። የሕይወት ተፈራ "Mine to Win" የተሰኘ ድርሰት መቼቱን በዐፄ ዮሓንስ ንግሥና ዘመን፣ በጎጃም/ጎንደር የቅኔ መማሪያ ደብሮች ያደረገ ልብወለድ ነው። ልቦለዱ የቅኔ ትምህርት ስርዓትን ያስተዋውቀናል፤ በበኩሌ የቅኔ ትምህርትን እና የቅኔ ሊቃውንት ታላቅነት ቀድሞ ከነበረኝ ግንዛቤ የበለጠ እንዲሆን አድርጎኛል። በተለይ የተዋነይ ዘ ጎንጅ (በውኑ ዓለም የነበረ ባለቅኔ) ተከታይዋ አምስት መሥመር ቅኔ መጽሐፍ የሚወጣት እንደሆነች ልቦለዱ አሳሰበኝ። ወይም በአጭሩ ብዙ ምዕራባውያን ስንት መጽሐፍ የጻፉለት ፍልስፍናን በአምስት መሥመር ይዟል። የቅኔው ትርጓሜ የመጽሐፍ ቅዱስን እና የመጽሐፍ ቅዱሱን ፈጣሪ ኅልውና ይሞግታል። “የአምን ወይገኒ ኵሉ ዓለም በዘፈጠረ ለሊሁ ብዙኃን እንዘ ይገንዩ ይስግዱ ቅድሜሁ ለነጽሮ ዝኒ ነገር እሥራኤል ከመይፍርሑ ሙሴ ፈጠረ ፈጣሪሁ ወ ፈጣሪ ፈጠረ ኪያሁ።” (ተዋነይ ዘ ጎንጅ። ምንጭ፣ሕይወት ታደሰ ወደአማርኛ የተረጎመችው የሕይወት ተፈራ መጽሐፍ) ትርጉሙን በኋላ እመለስበታለሁ። ስለተዋነይ መጀመሪያ የሰማሁት የበውቀቱ መጽሐፍ ላይ ነበር። እሱም በጨረፍታ - “የሌሊት ዜማዎች” የሚለው ግጥሙ ውስጥ። በውቀቱ ተዋነይን በግጥሙ ግርጌ ማስታወሻው አስተዋውቆን ያልፋል፣ “ተዋነይ በቅኔ ቤት አፈ ታሪክ ሞትን በግዝት ለሰባት ዓመታት ያቆመ ጀግና ነው"። ከዚያ በኋላ፣ አዲስ አድማስ ላይ የወጣ አንድ ጽሑፍ ተዋነይ የተላከበትን ...