Skip to main content

እስኪ እንጠያየቅ፤ አገራችን የት ነው? (መጠባበቂያ ካስፈለገ)


ከመቶ ዓመት በፊት፣ በሃገራችን ሸንጎዎች የሚካሔዱት በተጻፈ ሕግ ሳይሆን በዳኞቹ የብልሐት ፍርድ ነበር፡፡ በምኒልክ ዘመን በዳኝነት ጥበባቸው ስማቸው ደጋግሞ የሚነሱት ፊታውራሪ ኃብተጊዮርጊስ ናቸው፡፡ ካልተሳሳትኩ - ከዳኝነት ባንዱ የሚከተለው የገጠማቸውም እርሳቸው ናቸው፤ አንድ ሕፃን ልጅ ‹የኔ ነው፣ የኔ ነው› በሚል የተካሰሱ ሁለት ሴቶች ፍርዳቸውን ሽተው ቀረቡ፡፡

ኃብተጊዮርጊስ በጣም ተጨንቀው፣ አውጥተው፣ አውርደው ውሳኔያቸውን አሳለፉ፡፡ “እንግዲህ ሁለታችሁም እናት ነኝ ብላችኋል፡፡ ሁለታችሁም እናት መሆናችሁን ምስክር አቅርባችሁ አረጋግጣችኋል፡፡ እኔም ሁለታችሁም እናት መሆናችሁን አምኛለሁ፡፡ ስለዚህ ልጁ ለሁለት ተሰንጥቆ እኩል፣ እኩል እንድትካፈሉት ፈርጃለሁ፤” ብለው ወሰኑ፡፡

ውሳኔው እንደተላለፈ፣ አንደኛዋ ሴት ብትስማማም ሌላኛዋ ግን “በቃ ይቅርብኝ፣ ልጄ አይደለም፤ ትውሰደው” አለች፡፡ ይሄን ጊዜ ኃብተጊዮርጊስ “ልጁን ለመካፈል የተስማማችውን ሴት እንድትቀጣ ፈርደው ሲያበቁ፣ በልጇ መጨከን አቅቷት ‹ልጄ አይደለም› ለማለት ለበቃችው ሴት የእናትነት መብቷን አጎናጽፈዋታል፡፡

ከመቶ ዓመት በኋላስ?
አቶ ሽፈራው ሽጉጤ የደቡብ ሕዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት ናቸው፡፡ ስለእርሳቸው ሰሞኑን ብዙ ያነጋገረን ፍርደ-ገምድልነት ከማውራቴ በፊት ባለፈው ሰሞን ተወርቶ የከሰመውን ገመናቸውን ማስታወስ እፈልጋለሁ፡፡ ኢሕአዴግ በታሪኩ ያስተማረን ነገር ቢኖር፣ ለፓርቲው ታማኝ እስከሆኑ ድረስ የማይስተሰረይ ሃጢያት ብሎ ነገር የለም፡፡ ራሱ ኢሕአዴግ በቅርቡ በመሃላ እንዳረጋገጠልን የመንግስት ሌቦች ከመብዛታቸው የተነሳ፣ የሃገሪቱ ዋነኛ ችግር ሙስና ሆኗል፡፡ (በርግጥ እንደዛም ሆኖ ድህነት ቀንሷል፤ እኔም ብሆን በዚህ እስማማለሁ - ሙስና እስካለ ድረስ ድሃ የነበሩ ባለስልጣናት ሃብታም መሆናቸው አይቀርም፡፡)

አቶ ሽፈራው ሽጉጤ የካቲት 2004 ላይ በተካሄደው የደኢሕዴን ዓመታዊ ስብሰባ ላይ የሲዳማ ቡና ላኪዎች ማሕበር ባለአክሲዮን ናቸው፣ ሚሊዮን ብሮች መዝብረዋል የሚል ትችት ቀርቦባቸው÷ ‹ከተከሰስኩ ብቻዬን አይደለም ወ/ሮ አዜብ መስፍንም መከሰስ አለባት› ብለው ግምገማውን ረግጠው ወጥተዋል በሚል የተሰማውን የውስጥ አዋቂዎች ወሬ በርካታ ድረዓምባዎች ‹ነገሩ እንዴት ነው?› ብለውበታል፡፡ (ያኔ ኢሕአዴግ የኢትዮጵያ ችግር ሙስና መሆኑን በይፋ ሊያውጅ አንድ ወር ይቀረው ነበር፡፡) ነገርዬው እላይ ቤት በማነካካቱ ነው መሰለኝ ፍርዱ የውሃ ሽታ ሆኖ ቀርቷል፡፡

ተፈርዶባቸው የማያውቁት አቶ ሽፈራው ሽጉጤ በክልላቸው የሚኖሩ አማርኛ ተናጋሪ ሰዎች ላይ ለመፍረድ ግን እምብዛም የተቸገሩ አይመስልም፡፡

አቶ ሽፈራው ሽጉጤ፣ በአንድ ወቅት ለethiopiafirst ድረዓምባ ስለብሔር ፌዴራሊዝም ጠቃሚነት ሲያብራሩ እንዲህ ብለው ነበር፡-

“በዚህች አገር ላይ የነበርን ዜጎች ሁለት ዓይነት ዜጎች ነበርን፡፡ አንደኛ፡- እኛ ገዢ ነን ብለው የሚያምኑ፤ የገዢ መደቦች ያሉባት፤ ሁለተኛ፡- በሃገራቸው፣ በመሬታቸው፣ በምድራቸው የማይኮሩ፤ ሁለተኛ ዜጋ ሆነው ተቆጥረው የሚኖሩባት አገር ነች፡፡ ይሄ ሁኔታ ነው የተቀየረው አሁን፡፡…. ይህንን ይዘን ግን …በመከባበር፣ በመደጋገፍ፣ በእኩልነት መንፈስ አንዲት ታላቅ እና ጠንካራ ኢትዮጵያ መገንባት እንችላለን፡፡”

እርሳቸው ‹አንደኛ፤› ብለው የተናገሩትን ስሰማ ትዝ የሚለኝ ያለፈ ነገር አይደለም፡፡ የአሁኒቷ ኢትዮጵያ ናት፡፡ እንደዘረኝነት አትቁጠሩብኝና ‹አሁን፣ በኢትዮጵያ የገዢው ፓርቲ መደብ (ብሔር) ማነው?› ብዬ ብጠይቃችሁ በእያንዳንዳችሁ አእምሮ ውስጥ የሚውጠነጠነው የተለያየ መልስ ነው የሚል ስጋት የሚያድርብኝ ይመስላችኋል? በፍፁም እንዳይመስላችሁ፤ ሁላችንም የምንረዳው ሐቅ አንድ ነው፡፡

ለመሆኑ እርሳቸው ራሳቸው ‹በመከባበር፣ በመደጋፍ፣ በእኩልነት መንፈስ› ትገነባለች የሚሉን ኢትዮጵያ “አንተ የዚህ ቋንቋ ተናጋሪ ስለሆንክ በዚህ ክልል መኖር አትችልም፤” ብሎ ደብዳቤ በሚጽፍ ክልላዊ አስተዳደር እና የብሔር ፌዴራሊዝም ነው ብለው ያምናሉ? እርሳቸው ቢያምኑስ እኛ እንድናምናቸው ይፈልጋሉ?

ዛሬ የጉሬ ፌርዳ ሰዎች ናቸው በአስተዳደራቸው ቀጭን ትዕዛዝ ከቀያቸው በቋንቋቸው ጦስ የተሰናበቱት፡፡ ነገስ፤ ማነሽ ባለተራ?
------
ምንም እንኳን የፊታውራሪ ኃብተጊዮርጊስ የዳኝነት ታሪክ ብዬ የተረኩላችሁን አንድ መጽሃፍ ላይ እንዳነበብኩት በመጨረሻ ባስታውስም:: ታሪኩ በመጽሃፍ ቅዱስ ላይ የጠቢቡ ሰለሞን ታሪክ ሆኖ ተገኝቷል::

Comments

  1. FYI-check this story, read it from no 17-28. you will see the true story Of ፊታውራሪ ኃብተጊዮርጊስ .http://www.wordproject.org/am/11/3.htm

    ReplyDelete

Post a Comment

Popular posts from this blog

The "Corridor Development" is a Façade of the Prosperity Party

Befekadu Hailu I have seen a news report claiming that 40% of central Addis Ababa will be demolished for the corridor development; I am not able to confirm the validity of the news but it sounds real to me given the size of massive operations in the demolition of old neighborhoods and construction of bike lanes, green areas, and glittering street lights. I like to see some beauty added to my city but cannot help mourning the slow death of it too. Addis Ababa was already in a huge crisis of housing and the demolition of houses is exacerbating it. Apparently, Prime Minister Abiy Ahmed is eager to showcase his vision of prosperity by demonstrating how fast his administration can do magic by beautifying the front sides of the streets with lights, new pavements, and painted fences ("to fake it until he makes it" in my friend's words). Therefore, he and his party do not care about the miserable human stories behind the scenes and they will harass you if you tell it (Azeb Woku...

መጽሐፍ የሚወጣው፣ የተዋነይ ዘ ጎንጅ 5 መሥመር ቅኔ

ጎንጅ ቅኔ ያጠናበት ደብር ሥም ነው። ደብረ ጥበብ ጎንጅ ቅዱስ ቴዎድሮስ ገዳም። ተዋነይ የባለቅኔው ሥም ነው። (የግዕዝ ትርጉሙ "ዋናተኛ" ማለት ነው።) ሊቁ ተዋነይ የልኅቀቱን ያክል እምብዛም አይወራለትም፤ ነገር ግን በዘመኑ ወደር የሌለው ልኂቅ ስለመሆኑ ሥራው ይናገራል። የሕይወት ተፈራ "Mine to Win" የተሰኘ ድርሰት መቼቱን በዐፄ ዮሓንስ ንግሥና ዘመን፣ በጎጃም/ጎንደር የቅኔ መማሪያ ደብሮች ያደረገ ልብወለድ ነው። ልቦለዱ የቅኔ ትምህርት ስርዓትን ያስተዋውቀናል፤ በበኩሌ የቅኔ ትምህርትን እና የቅኔ ሊቃውንት ታላቅነት ቀድሞ ከነበረኝ ግንዛቤ የበለጠ እንዲሆን አድርጎኛል። በተለይ የተዋነይ ዘ ጎንጅ (በውኑ ዓለም የነበረ ባለቅኔ) ተከታይዋ አምስት መሥመር ቅኔ መጽሐፍ የሚወጣት እንደሆነች ልቦለዱ አሳሰበኝ። ወይም በአጭሩ ብዙ ምዕራባውያን ስንት መጽሐፍ የጻፉለት ፍልስፍናን በአምስት መሥመር ይዟል። የቅኔው ትርጓሜ የመጽሐፍ ቅዱስን እና የመጽሐፍ ቅዱሱን ፈጣሪ ኅልውና ይሞግታል። “የአምን ወይገኒ ኵሉ ዓለም በዘፈጠረ ለሊሁ ብዙኃን እንዘ ይገንዩ ይስግዱ ቅድሜሁ ለነጽሮ ዝኒ ነገር እሥራኤል ከመይፍርሑ ሙሴ ፈጠረ ፈጣሪሁ ወ ፈጣሪ ፈጠረ ኪያሁ።” (ተዋነይ ዘ ጎንጅ። ምንጭ፣ሕይወት ታደሰ ወደአማርኛ የተረጎመችው የሕይወት ተፈራ መጽሐፍ) ትርጉሙን በኋላ እመለስበታለሁ። ስለተዋነይ መጀመሪያ የሰማሁት የበውቀቱ መጽሐፍ ላይ ነበር። እሱም በጨረፍታ - “የሌሊት ዜማዎች” የሚለው ግጥሙ ውስጥ። በውቀቱ ተዋነይን በግጥሙ ግርጌ ማስታወሻው አስተዋውቆን ያልፋል፣ “ተዋነይ በቅኔ ቤት አፈ ታሪክ ሞትን በግዝት ለሰባት ዓመታት ያቆመ ጀግና ነው"። ከዚያ በኋላ፣ አዲስ አድማስ ላይ የወጣ አንድ ጽሑፍ ተዋነይ የተላከበትን ...

የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ

በፍቃዱ ዘ . ኃይሉ “የአዲስ አበባ ብሔርተኝነት” ቢኖር ኖሮ መሪው ልጅ ሚካኤል ይሆን ነበር። አሁን አሁን እሱ ስለ አዲስ አበባ የዘፈናቸውን ዘፈኖች ቁጥር ራሱ በትክክል መቁጠር ይቸግረኛል። ለአዲስ አበባ ከተዘፈኑ ዘፈኖቹ ውጪም በየዘፈኑ ውስጥ የሚጨማምራቸው መልዕክቶች በራሳቸው መወድሰ አዲስ አበባ ናቸው። ለምሳሌ፣ በቅርቡ በለቀቀው ‘አዲስ አራዳ’ በተሰኘው አልበሙ ውስጥ ‘የድሬ ልጅ’ የሚል ዘፈን አለው። ዘፈኑ የተዘጋጀው ያው የአዲስ አበባ እህት ተደርጋ የምትቆጠረውን ድሬ ዳዋን ለማወደስ ነበር። ልጅ ሚካኤል ግን የአዲስ አበባ ፍቅሩ ያመልጠውና የሚከተለውን ያቀነቅናል፦ “መጣልሽ በሏት፣ ድሬ ድረስ፣  ከአዱ ገነት፣ ከሸገር፣ ከአዲስ ደረሰ፣... የሸገር ልጅ አራዳ ነው፣ ሰው አክባሪ፣ ሰው ወዳዱ፣ ቀላጅና ተረበኛ፣ ፍቅር ይዞ የሚተኛ፣ ‘አለው’ የለ፣ ‘የለው’ የለ፣ ከሁሉ ጋ፣ ግባ ጀባ...፤” ፤ ልጅ ሚካኤል በዚህ አልበሙ ብቻ አዲስ አበባን የሚያውድሰባቸው ሌሎችም ዘፈኖች አሉ፤ ‘ አዲስ አራዳ ’ የሚለው የአልበሙ መጠሪያ እና ‘ሸገር’ የሚሉት ዘፈኖቹ ዋነኞቹ ናቸው። ታዲያ እንዲህ በአዲስ አበባ ፍቅር የሚቃጠለው ልጅ ሚካኤል "ሊነግረን የሚፈልገው ምንድን ነው?" የሚለው ጥያቄ ደጋግሞ ይመጣብኛል። ይህ የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ ምንነትን ለመረዳት የሚጥር ፖለቲካዊ መጣጥፍ ነው። ‘አዲሱ አራዳ’ ማነው? በዚህ ዘፈኑ በብዙዎቻችን ዕድሜ የትዝታ ማኅደር ውስጥ የሚገኙ ነገር ግን በአዲስ አበባ ልማት ሥም የፈረሱ እና እየተረሱ ያሉ ሰፈሮችን ሥም ያነሳሳል። ዘፈኑ በግጥሙም በዜማውም፣ የሐዘን እንጉርጉሮ ያለበት ነው። ምሳሌ እንውሰድ፦ “ጨርሰሽ ስትወጪ ከቡፌ ዳ’ላጋ፣ ጠብቂኝ እንዳልል፣ ቆመሽ መሐሙድ’ጋ፣ አገር ...