Monday, April 7, 2025

ውንብድና እና የአዲስ አበባ ዝምታ…

 (በፍቃዱ ኃይሉ) 


አዲስ አበባ ውስጥ ውንብድና ጨምሯል። ይህንን የምለው እንዲሁ በልምድ “ዛሬ ከትላንት ይከፋል” በሚል ዲስኩር ተጠልፌ አይደለም። በራሴ ደርሶ ስላየሁት ነው፤ ያውም በአንድ ዓመት ርቀት ውስጥ ሁለት ጊዜ የወንበዴዎች ጥቃት ሰለባ ሆኛለሁ፤ ገጠመኙ ከተማዬ ውስጥ በፍርሐት እና በድንጋጤ እንድንቀሳቀስ አስገድዶኛል (ዝርዝሩን ወደ በኋላ እነግራችኋለሁ)።


አዲስ አበባ ዕድሜ ልኬን የኖርኩባት እና ጓዳ ጎድጓዳዋን የማውቃት ከተማ ነች። አዲሳባ ውስጥ ያልሔድኩበት ሰፈር፣ አምሽቼ ያልገባሁበት ሰዓት አልነበረም። በፊት፣ በፊት ውንብድና አልነበረም እያልኳችሁ አይደለም። ድብን አድርጎ ነበር። ነገር ግን በጥቂት ጥንቃቄ ራሳችሁን ማዳን ትችሉ ነበር። አሁን ግን ዓይን ያወጣ፣ ጭካኔ የበዛበት፣ አልፎ ተርፎም ጥቂት ገንዘብ የሚያወጣ ስልክ ይዛችሁ እንደሁ ተስፋ በማድረግ፣ ሕይወታችሁን አደጋ ላይ የሚጥል “ጨቦ” (chokehold) ተደራጅተው በመኪና በሚንቀሳቀሱ ሰዎች የሚፈፀምበት፣ እና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣ ውንብድና ነው።


ለዚህ መጣጥፍ መነሻ የሆነኝ፣ ይኼ ቦሌ አካባቢ፣ ሁለት ሆነው የሚሔዱ ሰዎችን በመኪና የሚንቀሳቀሱ ሰዎች ከኋላቸው ሲያንቋቸው የሚያሳይ ቪዲዮ ነው። ቪዲዮው እንደሚያሳየው ቪዲዮው ከሚቀረፅበት አቅጣጫ የመኪና ጡሩንባ ሲጮህ ይደመጣል። ቀራጩ መኪናው ውስጥ ያለ ይመስላል። በዚህ ጊዜ ከወንበዴዎቹ አንዱ ወደ መኪናው ድንጋይ ይወረውርበታል። ሌላ መኪናም እንዲሁ መንገድ ሊዘጋባቸው ሲሞክር ነገር ይታያል። ውንብድናው እየተፈፀመ ያለው ተመልካች ባለበት ሁኔታ ነው። ሁለቱን ተጠቂዎች ያነቋቸው ወንበዴዎች ግን ዘረፋቸውን በዚህ ሁሉ ግርግር ሳይረበሹ አጠናቅቀዋል። ይህን ዓይነት ቪዲዮ ሳይ የመጀመሪያዬ አይደለም። በጣም በርካታ ተመሳሳይ ትራጄዲዎች በየማኅበራዊ ሚዲያው ተለጥፈዋል። 


የመጀመሪያ ጊዜ የተዘረፍኩት በሲኤምሲ አጥር በኩል በዋናው ጎዳና ላይ፣ ከምሽቱ 2:05 ሰዓት ገደማ ነበር። የመንገድ መብራት ቢኖርም በዛፎቹ ተከልሎ የእግረኛው መንገድ ደንገዝገዝ ብሏል። መኪኖች ውር ውር ይላሉ። ድንገት ከኋላዬ የሆነ ሰው አንገቴ ላይ ተጠመጠመብኝ። መጀመሪያ የመሰለኝ የሆነ መላፋት የሚወድ የልጅነት ጓደኛዬ ድንገት ሲያየኝ ዘሎ የተጠመጠመብኝ ነበር። ከዛ ሌላኛውን ሰው ከፊት ለፊቴ አየሁት። ነገርዬው ዝርፊያ እንደሆነ በገባኝ በቅፅበት ውስጥ የለሁም። ስነቃ፣ መሬት ላይ ተጋድሜያለሁ። በሰመመን “መሬት ላይ ለምን ተኛሁ?” እያልኩ ራሴን እጠይቃለሁ። ከዛ በአጠገቤ ሽው ሽው የሚሉ መኪኖች አሉ። ደንግጬ ተስፈንጥሬ ተነሳሁ። ሰውነቴ ትንሽ ተጋግጧል። ስልኬን እና ዋሌቴን ወስደውታል፤ ኪሴ ውስጥ የነበረው ትንሽ ገንዘብ ግን አልተወሰደም። በኋላ በአካባቢው የነበሩ ሰዎች የተናገሩትን ገጣጥሜ ስተነትነው ወንበዴዎቹ በመኪና የሚንቀሳቀሱ ናቸው። እኔን ሲያንቁ አንድ ሚኒባስ ታክሲ ሲመጣባቸው ራሴን እንደሳትኩ በቁሜ ጥለውኝ በያዙት መኪና ሸሽተው እንደሔዱ ገምቻለሁ። ሰውነቴ የተፋፋቀው በዛ ምክንያት መሰለኝ። የኪስ ገንዘቤን ያልወሰዱትም በዚያ ምክንያት ተጣድፈው ይመስላል። 


ይኼንን ገጠመኜን ስናገር በዙሪያዬ ያሉ ሰዎች በሙሉ ወይ በቅርቡ ደርሶባቸዋል አልያም የደረሰበት ሰው ያውቃሉ። የእኔም ታናሽ ወንድም ከጥቂት ዓመታት በፊት ተመሳሳይ ጥቃት ደርሶበት ነበር። እሱ ያውም ቀድሞ ነቅቶ ስለታገላቸው ትከሻው አካባቢ በጩቤ ወግተውታል። 


በጉዞ ገጠመኝ ከዚህ በፊት የጎበኘኋቸው አንዳንድ ከተሞች ውስጥ በጣም የሚያስፈሩ ታሪኮችን ስሰማ “አዲስ አበባ እኮ ገነት ናት” እያልኩ እናገር ነበር። ናይሮቢ እና ካምፓላ ውስጥ ትንንሽ የሰፈር ሱቆች መስኮታቸው በብረት ፍርግርግ ነው የሚጠበቀው። የመስታወት ሱቆች ያሉት ሞል ውስጥ ብቻ እንጂ መንገድ ዳር አይደለም። የኤቲኤም ማሽኖች በወታደር የሚጠበቁባቸው ቦታዎች አሉ። ጆሃንስበርግ ከተማ ዳር ዳሩ ላይ በእግር መንቀሳቀስ አይመከርም፤ ምክንያቱም የተደራጁ ወንበዴዎች ድንገተኛ የዘረፋ ጥቃት ሊፈፅሙባችሁ ይችላሉ። አዲስ አበባ እነዚህ ተርታ አልደረሰችም። ነገር ግን ወደዚያ እየተጓዘች ይመስለኛል። 


ሁለተኛውን ገጠመኜን ከማውራቴ በፊት ለምን ውንብድና እንዲህ ዓይን አወጣ የሚለው ላይ ጥቂት እንነጋገር። 

Friday, March 28, 2025

ግለሰብ፣ ፓርቲ፣ መንግሥት እና አገር

(በፍቃዱ . ኃይሉ)

አምባገነናዊ ስርዓቶች ግለሰብ፣ ፓርቲ፣ መንግሥት እና አገርን ለዜጎቻቸው እንደማይነጣጠሉ አስመስለው ያቀርባሉ። ግለሰቡን ከነካችሁ ፓርቲው ይፈርሳል፣ ፓርቲውን ከነካችሁ፣ መንግሥቱ ይፈርሳል፣ መንግሥቱን ከነካችሁ አገሩ ይፈርሳል። እውነት አላቸው። አምባገነኖች እና የአገዛዙ ጥቅመኞች ሕልውናቸውን ከአገሩ ሕልውና ጋር አስተሳስረው ነው የሚኖሩት። ኢሕአዴግ ከመውደቁ ትንሽ ሰሞን ቀደም ብሎ በአማርኛ ዝና ያገኘ አንድ የትግርኛ አባባል ነበርለምጣዱ ሲባል አይጧ ትትረፍ።በግለሰቦች እና አገዛዞች መተሳሰር ምክንያት ዜጎች አምባገነኖችን ለመጣል ሲታገሉ አገራቸውንም ራሳቸው ላይ ይማፍረስ ስጋት አላቸው። ስለዚህ አምባገነኖችን መታገል በጣም አስቸጋሪ ነው፤ ነገር ግን የማይቻል አይደለም።

የማይሻር ግለሰብ እና የማይቀየር የፖለቲካ ፓርቲ ያለበት መንግሥት መጨረሻው ለአገሩ ጠንቅ መሆን ነው። ግለሰቡም፣ ፓርቲውም ዘላቂ ዕድሜ የላቸውም። በመሆኑም ዜጎች መፃዒ ዕጣ ፈንታቸውን በሰቀቀን እንዲጠብቁ ይገደዳሉ። ተወደደም ተጠላም በብዙኃን ይሁንታ የሚወጣ እና የሚወርድ መንግሥት ያለበት አገር የተሻለ ተስፋና ሰላም ለሕዝቡ ይሰጣል። ነገር ግን በብዙኃን ይሁንታ መውጣት እና መውረድ ብቻ በቂ አይደለም። ገዢዎች በሥልጣን ላይ በሚቆዩበት ጊዜ ማድረግ የሚችሉት ነገር ካልተገደበ እያደር አውዳሚ ከመሆን አይመለሱም።

ይባስ ብሎ፣ በአምባገነናዊ ስርዓቶች ውስጥ ግን ሥልጣን ላይ መውጫ እና ሥልጣን ላይ መሰንበቻው መንገድ ነውጥ ብቻ ነው። ባለ ፍፁም ሥልጣኑ - አምባገነኑ - በወደቀ ቁጥር፣ ቢያንስ በየትውልዱ ትርምስ ይኖራል። አጥኚዎች ኢትዮጵያ ውስጥ ቢያንስ ላለፉት ሁለት መቶ ዓመታት፣ ትልቅ ጦርነት ያላየ ትውልድ የለም የሚሉት ለዚህ ነው።

መንግሥት በግለሰብ እጅ ተጠልፎ እንዳይወድቅ ለማድረግ የተፈጠረው ሞዴል ማዲሰኒያን ሞዴል ይባላል። ከአሜሪካ መንግሥት መሥራቾች መካከል ጄምስ ማዲሰን በጻፈው ጽሑፍ ላይ የተመሠረተ ሞዴል ነው። ሞዴሉ፣ ቢያንስ እስካሁን ለብዙ ዴሞክራሲያዊ አገሮች ሠርቷል።  የጀምስ ማዲሰን ጽሑፍ እንዲህ ይላል፤ሰዎች መልዓክ ቢሆኑ ኖሮ፥ መንግሥታት አያስፈልጉም ነበር። ሰዎችን የሚገዟቸው መላዕክት ቢሆኑም ኖሮ፥ መንግሥታት ላይ ቁጥጥር መጣል አያስፈልግም ነበር። ሰዎችን ሰዎች በሚያስተዳድሩበት ሁኔታ መንግሥትን መቅረፅ፥ ከባድ ፈተና አለበት። መጀመሪያ ገዢው ተገዢዎቹን መቆጣጠር መቻል አለበት፤ ከዚያ ገዢው ራሱን እንዲገዛ ማስገደድ ያስፈልጋል።” ("ፌዴራሊስት ፔፐርስ 51")

የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥትም የማዲሰንያንን ሞዴል ለመኮረጅ ሞክሯል። በመነባነብ እንደሚነገረው ሕግ አውጪ አለ (ፓርላማው) ሕግ ተርጓሚ አለ (ፍርድ ቤቶችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቱ) እንዲሁም አስፈፃሚ አካል አለ (ጠቅላይ ሚኒስቴሩ፣ ካቢኔው፣ የፀጥታ ኃይሉ፣ ወዘተ።) ነገር ግን ሁለቱ የመንግሥት ቅርንጫፎች የአስፈፃሚው አካል እስረኞች እንጂ ሚዛን ጠባቂዎች አይደሉም።

Sunday, October 20, 2024

የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ

(በፍቃዱ ዘ. ኃይሉ) 

“የአዲስ አበባ ብሔርተኝነት” ቢኖር ኖሮ መሪው ልጅ ሚካኤል ይሆን ነበር። አሁን አሁን እሱ ስለ አዲስ አበባ የዘፈናቸውን ዘፈኖች ቁጥር ራሱ በትክክል መቁጠር ይቸግረኛል። ለአዲስ አበባ ከተዘፈኑ ዘፈኖቹ ውጪም በየዘፈኑ ውስጥ የሚጨማምራቸው መልዕክቶች በራሳቸው መወድሰ አዲስ አበባ ናቸው። ለምሳሌ፣ በቅርቡ በለቀቀው ‘አዲስ አራዳ’ በተሰኘው አልበሙ ውስጥ ‘የድሬ ልጅ’ የሚል ዘፈን አለው። ዘፈኑ የተዘጋጀው ያው የአዲስ አበባ እህት ተደርጋ የምትቆጠረውን ድሬ ዳዋን ለማወደስ ነበር። ልጅ ሚካኤል ግን የአዲስ አበባ ፍቅሩ ያመልጠውና የሚከተለውን ያቀነቅናል፦

“መጣልሽ በሏት፣ ድሬ ድረስ፣

 ከአዱ ገነት፣ ከሸገር፣ ከአዲስ ደረሰ፣...

የሸገር ልጅ አራዳ ነው፣ ሰው አክባሪ፣ ሰው ወዳዱ፣

ቀላጅና ተረበኛ፣

ፍቅር ይዞ የሚተኛ፣

‘አለው’ የለ፣ ‘የለው’ የለ፣

ከሁሉ ጋ፣ ግባ ጀባ...፤”

ልጅ ሚካኤል በዚህ አልበሙ ብቻ አዲስ አበባን የሚያውድሰባቸው ሌሎችም ዘፈኖች አሉ፤ ‘አዲስ አራዳ’ የሚለው የአልበሙ መጠሪያ እና ‘ሸገር’ የሚሉት ዘፈኖቹ ዋነኞቹ ናቸው። ታዲያ እንዲህ በአዲስ አበባ ፍቅር የሚቃጠለው ልጅ ሚካኤል "ሊነግረን የሚፈልገው ምንድን ነው?" የሚለው ጥያቄ ደጋግሞ ይመጣብኛል። ይህ የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ ምንነትን ለመረዳት የሚጥር ፖለቲካዊ መጣጥፍ ነው።


‘አዲሱ አራዳ’ ማነው?
በዚህ ዘፈኑ በብዙዎቻችን ዕድሜ የትዝታ ማኅደር ውስጥ የሚገኙ ነገር ግን በአዲስ አበባ ልማት ሥም የፈረሱ እና እየተረሱ ያሉ ሰፈሮችን ሥም ያነሳሳል። ዘፈኑ በግጥሙም በዜማውም፣ የሐዘን እንጉርጉሮ ያለበት ነው። ምሳሌ እንውሰድ፦

“ጨርሰሽ ስትወጪ ከቡፌ ዳ’ላጋ፣

ጠብቂኝ እንዳልል፣ ቆመሽ መሐሙድ’ጋ፣

አገር ተቀይሯል፣ ተኝቼ ሲነጋ”

Monday, October 14, 2024

The "Corridor Development" is a Façade of the Prosperity Party

(Befekadu Hailu) 

I have seen a news report claiming that 40% of central Addis Ababa will be demolished for the corridor development; I am not able to confirm the validity of the news but it sounds real to me given the size of massive operations in the demolition of old neighborhoods and construction of bike lanes, green areas, and glittering street lights. I like to see some beauty added to my city but cannot help mourning the slow death of it too.

Addis Ababa was already in a huge crisis of housing and the demolition of houses is exacerbating it.

Apparently, Prime Minister Abiy Ahmed is eager to showcase his vision of prosperity by demonstrating how fast his administration can do magic by beautifying the front sides of the streets with lights, new pavements, and painted fences ("to fake it until he makes it" in my friend's words). Therefore, he and his party do not care about the miserable human stories behind the scenes and they will harass you if you tell it (Azeb Woku's case in point). The corridor development is a façade because, however beautiful and bright they look from the outside, there are untold, ugly, and sad stories from behind.

The new pavement down the area formerly known as Mahmoud. 
A façade is defined as "an outward appearance that is maintained to conceal a less pleasant or creditable reality", exactly what the corridor development is about.

The corridor development is happening without MEANINGFUL consultation of affected communities and experts. People are displaced without proper notice, without timely relocation or resettlement, and without a majority's consent. Experts are appalled by the recreation of the city with disregard for its history, geography, and economy. It is a spontaneous, random, copycat of foreign cities without enough planning and reasonable time of construction that compromised quality. The long-term outcome of the development activity for the city and its economy remains contested and left to fate. The corridor development prioritizes showing off glittering streets while destroying resilient communities. The neighborhoods of Addis Ababa have strong communities that function within successive and concurrent failures of regimes to alleviate poverty. The informal economies that the communities built up and helped them persevere bad days are broken overnight due to it. In the new lives these communities are forced to live, there is no social support system that they can rely on to survive the bad days as they did together before. 

Tuesday, June 25, 2024

From Sexist to Feminist: If I could do it, anyone can too

 This piece is inspired by a conversation between Soli and Tsion, two political women in Ethiopia, on Ajrit podcast. Ajrit podcast is run by Addis Powerhouse, a feminist online advocacy platform. In this episode, Soli refers to an article she and Mahi wrote on Zone 9 blog and received a response from myself and Endalk, along with others. Soli stressed how ridiculous we were in our response and was forced to revisit it. I still didn't recover from the embarrassment of learning that I used to think like that. 

Sunday, June 2, 2024

Short-Lived Victory: A Case of Mistaken Progress

 (Befekadu Hailu)


My friends and myself, who passed through Maekelawi's torturous experience, along with others campaigned and had the government decide to close the most notorious Detention Center that live three regimes and almost half a century in Ethiopia. In February 2019, Five years after I was detained and tortured in Maekelawi, I went to the closing Center to fetch my laptop confiscated five years before. I arrived while the name tag of the Center was being shattered and one of the uniformed guards said to me, “you have this place closed”; I shrugged like ‘proudly’. That little moment gave me a sense of victory, telling me that the activism and its subsequent sacrifice was not in vain. I felt we actually effected a change. Six years later, I started to doubt it all retrospectively. 


The political transition that started six years ago is known by many as ‘the change’ (lewtu in Amharic), but what really explains it is ‘the violence’ (newtu in Amharic). 


How Did We Get Here? 


I have gotten the chance to take part in the Human Rights Forum 2024 hosted by The Carter Center in the third week of May 2024 in Atlanta, US. In my keynote address, I have spoken to participants with my reflection on the works of human rights defenders based on my experience in Ethiopia. I don’t know how resonating my speech was to the audience but it was my moment to pause and reflection. 


Telling the story of how fast we dived from optimism to pessimism, I said: 


“After 2018, the growing expectations of human rights defenders were dashed by a false promise of change. 


“Retrospectively speaking, Ethiopian HRDs are not the only ones to lose momentum for a false promise of change. In the MENA region, most of the revolutions of 2011 have led to worse crises in their respective countries.  


“Ethiopia's neighboring Sudan had had a very exciting street revolution against Omar al-Bashir’s 26 years of dictatorship. A couple of years later, two power mongering generals are waging war on each other and their people. In all their defense, the Sudanese activists have tried their best to ensure the establishment of a civil government but it was not as easy.  


“The point is - we, human rights defenders, can force changes in protests or pressures; but, our commitment to maintain the changes with principles remains weak. We get fragmented, our priorities fast change, we retire early, we get burned out, we trust people in power forgetting that power corrupts people, and most importantly we forget that there won’t be democratization without the institutions. Then, we have the changes stolen and regret them.”

Tuesday, September 20, 2022

The Smear Campaign Against the Smallest Attempt to Pacificism in Ethiopia

My observation of the repressive culture of political groups in order to monopolize the political narrative in and around Ethiopia. 

As I mostly do, I write this piece to express my frustration, not my surprise. 

Recently, starting in mid-August 2022, a few civil society organizations leaders have gathered to consult to make our voices for peace collectively; for sustainable peace. To come up with a shared statement was not an easy task to do. We have done it on the eve of the Ethiopian new year in early September 2021 and it was difficult; it is difficult again a year later even though for the past few months, major warring parties in the Tigray war, have silenced their guns for humanitarian truce after the Ethiopian government unilaterally declared and the TPLF later accepted it conditionally. Even though the guns were temporarily silenced, the war propaganda was escalating slowly. We were worried because if the war starts again, we are going back to the era which is worse than we are in. That time, even though a peacebuilding process didn't start, at least people were not dying on daily basis. Therefore, we wanted to be stronger in our calls. The purpose was to renew the peace call from last year but also to actually encourage involved parties to resume their peace talk and stop the heated exchange of words. 

In the planning meeting, everyone has their own interpretation of words and phrases to be used. Everyone is overly concerned about how that party or this party misunderstands our messages; we are worried about the reactions of the media, social media, and every other stakeholder. We didn't want the controversies over anecdotes to cover the message. We thought it is our chance to make 'peace' at the epic center of the political discourse. By doing so, we thought we can make violent conflicts difficult for any party that might choose it. 

We have managed to reach the last draft and started to disseminate it to other CSOs who want to endorse it via email. The number of signatories started to grow and we have finally reached 35. Last year, only 24 CSOs have signed on it. This year, on May 3 when we renewed the call to hold on to the humanitarian truce with a call for sustainable peace and unfettered access to media freedom, we have 20 signatories. This is by far the biggest number but we didn't do enough effort, to keep it growing. We were competing with time. We believe people have had enough to reach the fatigue of war. 

ውንብድና እና የአዲስ አበባ ዝምታ…

  (በፍቃዱ ኃይሉ)  አዲስ አበባ ውስጥ ውንብድና ጨምሯል። ይህንን የምለው እንዲሁ በልምድ “ዛሬ ከትላንት ይከፋል” በሚል ዲስኩር ተጠልፌ አይደለም። በራሴ ደርሶ ስላየሁት ነው፤ ያውም በአንድ ዓመት ርቀት ውስጥ ሁለት ጊዜ...