Skip to main content

አብዮት ወረት ነው!


ከአብዮት ስሜት ቀመሱ (‹‹የተቀለበሰው አብዮት›› ብንለውም ችግር የለውም) ምርጫ 97 ወዲህ በርካታ ኩነቶች ተከስተዋል፡፡ መንግሰት ሁለተኛ ያንን ዓይነት ገጠመኝ እንዳይከሰት ቀዳዳዎችን ሁሉ በመድፈን ሥራ ተጠምዷል፤ ተቃዋሚዎችም በበኩላቸው ያንን ዓይነት ገጠመኝ ድጋሚ ለመፍጠር የቻሉትን ያህል ደክመዋል፡፡ እስካሁን ባለው ሒደት የመንግስት ሙከራ የተሳካ ይመስላል፡፡

የብዙዎች ጥያቄ፡-
‹‹ሕዝቡ ምን ነካው? ጭቆና ተስማምቶት ነው? ፈርቶ ነው? በተቃዋሚዎች እምነት አጥቆ ነው? ወይስ...?››

በርግጥ ለነዚህ ጥያቄዎች የሚሆን አጥጋቢ መልስ ለማቅረብ ሰማንያ ሚሊዮን ሕዝብን ያካተተ ጥናት ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ጥናት ሳያደርጉ (በኔ የማስተዋል ደረጃ) የግልን ግምገማ ብቻ በማስቀደም ሊደረስበት የሚችለውን ድምዳሜ ነው እዚህ የማስነብባችሁ፡፡

አብዮት ምንድን ነው?

አብዮት - ከዚህ ቀደም እንዳወራነው - የእንግሊዝኛውን Revolution እንዲተካ ‹‹በደርግ›› የተመረጠ፣ የግዕዙን ቃል ‹አበየ› (Revolut) መሠረት አድርጎ የተሰየመ ቃል ነው፡፡ አብዮት - መንግሰትን ወይም ርዕዮተ ዓለምን የመተካት ሒደት ነው፤ አብዮት - ድንገታዊ እና ፈጣን ክስተት ነው፡፡

አብዮት እያንዳንዱ ትውልድ ቢያንስ አንዴ ሊያልፍበት የሚገባ ከድሮ ተነስቶ ዘንድሮ ላይ የሚያርፍበት ድልድይ ነው፡፡ አብዮት የታመቀ የሕዝብ ጩኸት የሚፈነዳበት አጋጣሚ ነው፡፡

አብዮት ድንገተኛ እና ፈጣን ክስተት ቢሆንም መሪ አለው፡፡ እንደምሳሌ የምርጫ 97ቱን ‹‹የተቀለበሰ አብዮት›› ብንመለከት÷ የቅንጅት አመራሮቸን እንደመሪ ልንመለከታቸው እንችላለን፡፡ በርግጥ አብዮት ተከታይ የለውም፡፡ ለዚህም ነው በዚሁ ምርጫ ወቅት ሕዝቡ ንቁ ተሳታፊ፣ አደራጊ ፈጣሪ ሆኖ የተስተዋለው፡፡ የሚደግፈውን አካል (ቅንጅትን) ስሜት ሲመራ የነበረው - በዚህ የመሪነት ሚና ነው፡፡

‹‹ያ አብዮት ባይቀለበስ›› ኖሮ÷ ሕዝቡ ይመጣል ብሎ የሚያስበውን ለውጥ እንዲያመጡ በአደራ የሚያስረክባቸው አካላት አሉት፣ ይመጣል ብሎ የሚያስበው ለውጥም አለ፡፡ እንዳለመታደል ሆኖ የዛኔው አብዮት ሳይሳካ በመቅረቱ ይህ ትውልድ እስካሁን ድረስ አብዮት እንደናፈቀው ቀርቷል፡፡ ነገር ግን ትውልዳዊ ግዴታ ነውና ‹‹መፈንዳቱ›› አይቀሬ ነው፡፡

አሁን በፌስቡክ አብዮት ‹‹ያፈነዳሉ›› ተብለው የተፈጠሩ በርካታ አባላት ያሏቸው፣ ብዙ ቡድኖች አሉ፡፡ እነዚህ የተናጠል እርምጃዎች ግን መሠረታዊ የአብዮት ባሕሪ እንደሚጎድላቸው ለመረዳት ብዙ ማሰብ አያስፈልገንም፡፡ እነዚህ የፌስቡክ አብዮት አማጪ ቡድኖች፡-

  1. መሪ የላቸውም፡- በርካታ የአብዮት ጥሪዎች ተካሒደዋል፡፡ እንዲያውም አንዳንዶቹ ሕዝባዊ ነውጥ የሚጀመርበትን ቀን ቆርጠው ነበር፡፡ ለምን ከሸፉ? ምክንያቱም ያ ቀን የተቆረተለትን አብዮት እንዲጀምሩ ሕዝቦች ቢጋበዙም - ቀን የቆረጡት ሰዎች ማንነት በውል አይታወቅም? ቢታወቅም አብዮት ከሕዝቡ ጋር ተቀላቅለው ሊመሩት አልተዘጋጁም? ቢዘጋጁም አብዮቱን ተከትሎ ሊመጣ የሚችለው የለውጥ ዓይነት ምን እንደሆነ? ማን እንደሚተካ እና እንዴት እንደሚተካ በግልጽ ያሳወቁበት መንገድ የለም፡፡ አብዮት የሕዝብ ጥያቄ በሕዝብ የሚቀርብበት እና መልሱም በሕዝብ ግፊት የሚገኝ ቢሆንም፣ አስፈፃሚዎቹ ጥቂቶች ናቸው፣ መሆንም አለባቸው፡፡ ሁሉም ሰው አስፈፃሚ መሆን አይችልምና!
  2. መንስኤ የላቸውም፡- ሕዝብ የተጠራቀመ ብሶት ሊኖረው ይችላል፡፡ ሆኖም ሕዝብ አብዮት እያሰበ አይኖርም፡፡ ሕዝብ ኑሮውን ለማሸነፍ ሲፍጨረጨር ብዙ ነገሮችን ሊያመልጡት ይችላል፡፡ አዋጆች አይሰማም፤ ሌላው ቀርቶ የኑሮው ማሽቆልቆል የአስተዳደር ችግር ውጤት መሆኑን አያስተውልም፡፡ ስለዚህ አብዮት በቀጠሮ የሚቀሰቀስ ሳይሆን የሆነ መንስኤን ተከትሎ የሚቀሰቀስ (‹‹የሚፈነዳ››) ሲሆን÷ ያንን መንስኤ ደግሞ እንደመልካም አጋጣሚ በመቁጠር ተቃውሞው ግለቱን እየጨመረ ሄዶ የመንግስትን መቀመጫ የሚያናጋ እንዲሆን የሚያደርግ ጠንካራ ቡድን ያስፈልጋል፡፡ ግን እሰካሁን መንስኤዎችን የሚገጠም የተዘጋጀ ቡድን የለም!
  3. አቀንቃኞች የሉም፡- አብዮት እንዲቀሰቀስ ሕዝቡ የሚያምንባቸው፣ ያሁኑን ክፉ፣ የመጪውን ደግሞ ደግ ቁልጭ ባለ አገላለፅ የሚያሳዩ፣ ወኔያቸው የማይበርድ፣ ጀግንነታቸው የሚጋባ አቀንቃኞች (activists) ያስፈልጋሉ፡፡ በመሠረቱ አብዮት የሚቀነባበረው በነዚሁ አቀንቃኞች ነው፡፡ በእኛ አገር (በተለይም በፌስቡክ) የምናያቸው ‹‹አቀንቃኞች›› አንዳንዶቹ ጭፍን ጥላቻን የሚነዙ፣ አንዳንዶቹ በእውነተኛ ስማቸው እና ማንነታቸው የማይታወቁ፣ አንዳንዶቹ ከሃገር እና ሃገራዊ አጀንዳዎች የራቁ - በጥቅሉ እምነት የሚጣልባቸው ዓይነት አይደሉም፡፡

እነዚህና መሰል ችግሮች በአሁኑ ይዘቱ፣ ፌስቡክን በጥቅሉ ወይም እስካሁን የተፈጠሩትን ቡድኖች በተለይ አብዮት ለመቀስቀስ የሚችል ብቃት ላይ አያስቀምጣቸውም፡፡ ነገር ግን የተደራጁ፣ ግልፅ አካሄድ እና ዓላማ ያላቸው የአቀንቃኞች ቡድን ራሱን አዘጋጅቶ - መፍጠር የሚገባውን ብሔራዊ ግንዛቤ እየፈጠረ መቆየት ከቻለ - አብዮት ወረት ነው - አንዴ ከተቀሰቀሰ ያልሰማው ላልሰማው እያስተላለፈ - እንደ ሰደድ እሳት ሃገሩን በሙሉ ማቀጣጠል ይችላል፡፡

ብዙዎች የኢትዮጵያ የፌስቡክ ማሕበረሰብ አንድ ሚሊዮን እንደማይሞላ፣ ካለውም ውስጥ ፖለቲካዊ ዒላማ ያለው ከአሥር ሺኅዎች እንደማይዘል አበክረው ይናገራሉ፡፡ እውነት ነው፡፡ ቢሆንም በዓለማችን ግዙፍ የተባሉ አብዮቶች በሙሉ የተለኮሱት ማሕበረሰቦቹ ውስጥ ንቃት ያላቸው፣ ጥቂት ከተሜ ወጣቶች ቡድን አማካይነት ነው፡፡

የንጉሣዊውን ሥርዓት የገረሰሰው አብዮት የተለኮሰው በተማሪዎች አማካይነት ነው፡፡ ጥያቄው ግን የብዙሐኑ ገበሬ እና ጭሰኞች ነበር፡፡ የዛን ጊዜው አብዮት የፊውዳሉን ሥርዓት በመደምሰስ ወደ ‹ሕብረተሰባዊነት› ተሸጋግሯል፡፡ ኢሕአዴግ ደርግን ሲጥል የነበረው ሒደት ከጥንት ጀምሮ የበረታው ነፍጠኛ፣ የደከመውን እያሸነፈ ራሱን ከሚያነግስበት የረዥም ጊዜ የትግል ውጤት የተለየ አይደለም፡፡ ስለዚህ አብዮት ልንለው አንችልም፡፡

የአሁኑ ትውልድ የሚያስፈልገው አብዮት የዚያን አይነት ብረት-መር ለውጥ አይደለም፡፡ አሁን ሕዝቡ የተጠማው ሰላማዊ፣ ያለ ደም መፋሰስ የሕዝቡን ፈቃድ ለሚፈፅም አካል ኃላፊነቱን ማስረከብ ነው፡፡ ይህንን ከግብ ለማድረስ ከዚህ በፊት (በምርጫ 97) ሞክሮ አልተሳካለትም፡፡ በምርጫ ያለው ተስፋ በመሟጠጡ በተቃውሞ አብዮት ሌላ ሥርዓት የመተካት ፍላጎት መኖሩ ተፈጥሯዊም አይቀሬም ነው፡፡ በዚህ ጽሁፍ መግቢያ ላይ ስለሕዝቡ ለቀረቡት ጥያቄዎች ትክክለኛ መልስ ሊሆን የሚችለው የሚከተለው ነው፡-
‹‹ግለሰቦች ሊልቁ ይችላሉ፤ የሚበጀውን የሚያውቀው ግን ሕዝቡ ነው፡፡ ሕዝብ ጭቆና አይስማማውም፣ ነገር ግን የተሻለ አማራጭ የሚመስለውን እሰከሚያይ ድረስ ዝም ብሎ ኑሮውን ይኖራል፡፡››

ስለዚህ ፌስቡክ ላይ የምናገኛቸው÷ በአብዛኛው - ወጣት፣ ከተሜ እና የተሻለ የትምህርት እና የመረጃ ዕድል ያገኙ ወጣቶችን ነው፡፡ የተበጣጠሰውን የነዚህን ወጣቶች ኃይል ወደአንድ መሰብሰብ ቢቻል÷ እንኳን ሃገራዊ ዓለምአቀፋዊ አብዮት መቀስቀስ ይቻላል፡፡ ስለዚህ በፌስቡክ አብዮት ተስፋ ለመቁረጥ ጊዜው ገና ነው÷ ነገር ግን መሠራት የሚገባው ብዙ ሥራ መኖሩን ተገንዘበው አብዮተኞች ‹‹ከተነሥ፣ አምፅ›› ጩኸታዊ ውትወታ ወደትርጉም አዘል ‹‹ስትራቴጂ ነደፋ›› እንዲገቡ እመክራለሁ፡፡

Comments

  1. ግሩም ጽሑፍ፡፡ብረት-መር አብዬትን መቃወምህ ይደገፋል፡፡ የነጥቦችህ ሎጂካል ቅደም ተከተል ግን…መንስዔ…አቀንቃኝ…እና መሪ ቢሆን ይሻለኛል፡፡
    የመንስዔ ነጥብህ ትክክል ነው፡፡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ እያለን ‹‹ምግባችን ይሻሻል›› ‹‹ወጡ አልጣፈጠንም›› ብለን ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተን ጥያቄያችን ድንገት ወደ ‹‹ሥርዓተ ትምህርት ይሻሻል›› ጥያቄ እንደተቀየረ አስታውሳለሁ፡፡
    ከዚያ ዓይናችን እያየ ያ ግብታዊ ሰላማዊ ሰልፍ መፈክር ባዬችን፤ ዘፋኞችን፤ ተናጋሪዎችን ፈጠረ (በጽሑፍ አቀንቃኝ ያልካቸው ይመስላሉ)፡፡
    መጨረሻ ግን የዩኒቨርሲቲው ሴኔት የቀረቡት፤ በተማሪው የተሞገሱት፤ በኋላም የተቀጡት ጥቂት ተማሪዎች ናቸው፡፡ አንዱም ተባረረ፡፡ መሪዎችም በአብዬት ይፈጠራሉ እንጂ አብዬትን አይፈጥሩም የሚል አስተያየት አለኝ፡፡ መሪ አብዬትን ከፈጠረማ፤ መሪ ራሱ መንስዔ ሆነ ማለት ነው፡፡ ይሄ ደግሞ ሌላ ፍልስፍናዊ ሙግት ያስነሳል መሰለኝ…

    ReplyDelete

Post a Comment

Popular posts from this blog

The "Corridor Development" is a Façade of the Prosperity Party

Befekadu Hailu I have seen a news report claiming that 40% of central Addis Ababa will be demolished for the corridor development; I am not able to confirm the validity of the news but it sounds real to me given the size of massive operations in the demolition of old neighborhoods and construction of bike lanes, green areas, and glittering street lights. I like to see some beauty added to my city but cannot help mourning the slow death of it too. Addis Ababa was already in a huge crisis of housing and the demolition of houses is exacerbating it. Apparently, Prime Minister Abiy Ahmed is eager to showcase his vision of prosperity by demonstrating how fast his administration can do magic by beautifying the front sides of the streets with lights, new pavements, and painted fences ("to fake it until he makes it" in my friend's words). Therefore, he and his party do not care about the miserable human stories behind the scenes and they will harass you if you tell it (Azeb Woku...

መጽሐፍ የሚወጣው፣ የተዋነይ ዘ ጎንጅ 5 መሥመር ቅኔ

ጎንጅ ቅኔ ያጠናበት ደብር ሥም ነው። ደብረ ጥበብ ጎንጅ ቅዱስ ቴዎድሮስ ገዳም። ተዋነይ የባለቅኔው ሥም ነው። (የግዕዝ ትርጉሙ "ዋናተኛ" ማለት ነው።) ሊቁ ተዋነይ የልኅቀቱን ያክል እምብዛም አይወራለትም፤ ነገር ግን በዘመኑ ወደር የሌለው ልኂቅ ስለመሆኑ ሥራው ይናገራል። የሕይወት ተፈራ "Mine to Win" የተሰኘ ድርሰት መቼቱን በዐፄ ዮሓንስ ንግሥና ዘመን፣ በጎጃም/ጎንደር የቅኔ መማሪያ ደብሮች ያደረገ ልብወለድ ነው። ልቦለዱ የቅኔ ትምህርት ስርዓትን ያስተዋውቀናል፤ በበኩሌ የቅኔ ትምህርትን እና የቅኔ ሊቃውንት ታላቅነት ቀድሞ ከነበረኝ ግንዛቤ የበለጠ እንዲሆን አድርጎኛል። በተለይ የተዋነይ ዘ ጎንጅ (በውኑ ዓለም የነበረ ባለቅኔ) ተከታይዋ አምስት መሥመር ቅኔ መጽሐፍ የሚወጣት እንደሆነች ልቦለዱ አሳሰበኝ። ወይም በአጭሩ ብዙ ምዕራባውያን ስንት መጽሐፍ የጻፉለት ፍልስፍናን በአምስት መሥመር ይዟል። የቅኔው ትርጓሜ የመጽሐፍ ቅዱስን እና የመጽሐፍ ቅዱሱን ፈጣሪ ኅልውና ይሞግታል። “የአምን ወይገኒ ኵሉ ዓለም በዘፈጠረ ለሊሁ ብዙኃን እንዘ ይገንዩ ይስግዱ ቅድሜሁ ለነጽሮ ዝኒ ነገር እሥራኤል ከመይፍርሑ ሙሴ ፈጠረ ፈጣሪሁ ወ ፈጣሪ ፈጠረ ኪያሁ።” (ተዋነይ ዘ ጎንጅ። ምንጭ፣ሕይወት ታደሰ ወደአማርኛ የተረጎመችው የሕይወት ተፈራ መጽሐፍ) ትርጉሙን በኋላ እመለስበታለሁ። ስለተዋነይ መጀመሪያ የሰማሁት የበውቀቱ መጽሐፍ ላይ ነበር። እሱም በጨረፍታ - “የሌሊት ዜማዎች” የሚለው ግጥሙ ውስጥ። በውቀቱ ተዋነይን በግጥሙ ግርጌ ማስታወሻው አስተዋውቆን ያልፋል፣ “ተዋነይ በቅኔ ቤት አፈ ታሪክ ሞትን በግዝት ለሰባት ዓመታት ያቆመ ጀግና ነው"። ከዚያ በኋላ፣ አዲስ አድማስ ላይ የወጣ አንድ ጽሑፍ ተዋነይ የተላከበትን ...

የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ

በፍቃዱ ዘ . ኃይሉ “የአዲስ አበባ ብሔርተኝነት” ቢኖር ኖሮ መሪው ልጅ ሚካኤል ይሆን ነበር። አሁን አሁን እሱ ስለ አዲስ አበባ የዘፈናቸውን ዘፈኖች ቁጥር ራሱ በትክክል መቁጠር ይቸግረኛል። ለአዲስ አበባ ከተዘፈኑ ዘፈኖቹ ውጪም በየዘፈኑ ውስጥ የሚጨማምራቸው መልዕክቶች በራሳቸው መወድሰ አዲስ አበባ ናቸው። ለምሳሌ፣ በቅርቡ በለቀቀው ‘አዲስ አራዳ’ በተሰኘው አልበሙ ውስጥ ‘የድሬ ልጅ’ የሚል ዘፈን አለው። ዘፈኑ የተዘጋጀው ያው የአዲስ አበባ እህት ተደርጋ የምትቆጠረውን ድሬ ዳዋን ለማወደስ ነበር። ልጅ ሚካኤል ግን የአዲስ አበባ ፍቅሩ ያመልጠውና የሚከተለውን ያቀነቅናል፦ “መጣልሽ በሏት፣ ድሬ ድረስ፣  ከአዱ ገነት፣ ከሸገር፣ ከአዲስ ደረሰ፣... የሸገር ልጅ አራዳ ነው፣ ሰው አክባሪ፣ ሰው ወዳዱ፣ ቀላጅና ተረበኛ፣ ፍቅር ይዞ የሚተኛ፣ ‘አለው’ የለ፣ ‘የለው’ የለ፣ ከሁሉ ጋ፣ ግባ ጀባ...፤” ፤ ልጅ ሚካኤል በዚህ አልበሙ ብቻ አዲስ አበባን የሚያውድሰባቸው ሌሎችም ዘፈኖች አሉ፤ ‘ አዲስ አራዳ ’ የሚለው የአልበሙ መጠሪያ እና ‘ሸገር’ የሚሉት ዘፈኖቹ ዋነኞቹ ናቸው። ታዲያ እንዲህ በአዲስ አበባ ፍቅር የሚቃጠለው ልጅ ሚካኤል "ሊነግረን የሚፈልገው ምንድን ነው?" የሚለው ጥያቄ ደጋግሞ ይመጣብኛል። ይህ የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ ምንነትን ለመረዳት የሚጥር ፖለቲካዊ መጣጥፍ ነው። ‘አዲሱ አራዳ’ ማነው? በዚህ ዘፈኑ በብዙዎቻችን ዕድሜ የትዝታ ማኅደር ውስጥ የሚገኙ ነገር ግን በአዲስ አበባ ልማት ሥም የፈረሱ እና እየተረሱ ያሉ ሰፈሮችን ሥም ያነሳሳል። ዘፈኑ በግጥሙም በዜማውም፣ የሐዘን እንጉርጉሮ ያለበት ነው። ምሳሌ እንውሰድ፦ “ጨርሰሽ ስትወጪ ከቡፌ ዳ’ላጋ፣ ጠብቂኝ እንዳልል፣ ቆመሽ መሐሙድ’ጋ፣ አገር ...