Skip to main content

የአሜሪካ ኮንግረስ እና ሌሎችም ከኢትዮጵያ ፓርላማ መማር የሚገባቸው!


(የዓለማችንን ሕዳሴ ለማፋጠን የቀረበ ምክረ ሐሳብ) እስከዛሬ የጻፍኳቸው ሁሉ የግል አቋሜን የሚያንጸባርቁ አልነበሩም፡፡ ነገርዬዎቹ “ኪራይ ሰብሳቢ” የተባለ ሰይጣን ለክፎኝ የተናገርኳቸው ነበሩ፡፡ ሰይጣኑ የለከፋቸው ሰዎች በኢትዮጵያ የተገነቡት ፎቆችና መንገዶች፣ የሰፈነው መልካም አስተዳር፣ በ11.4% የሚመነደገው ኢኮኖሚ አይታያቸውም፡፡ ለነሱ የሚታያቸው ድንጋይ ሲወረውሩ÷ ፓሊሶች ራሳቸውን ለመከላከል በሚተኩሱት ጥይት የሚሞቱ አደገኛ ቦዘኔዎች፣ ከስንት አንዴ የሚገለበጡ የምርጫ ኮሮጆዎች፣ የመንግስትን ሕልውና በስክርቢቶና ወረቀት የሚያናጉ ጋዜጠኞች መታሰር፣ የኢኮኖሚውን ዕድገት ተከትሎ የተከሰተው የዋጋ ግሽበት ብቻ ነው፡፡

ቻይናዊው ዕውቅ ኮሚኒስትና የፖለቲካ ጠቢብ ኪል ሃንግ÷ ጥርነፋ ወከመ ለስልጣን በሚል ርዕስ በጻፉት መጽሃፋቸው ላይ በኪራይ ሰብሳቢ ሰይጣን የተለከፉ ዜጎች ነፃ ሊወጡ የሚችሉባቸውን መንገዶች ሦስቱ ‘መ’ዎች በማለት ሰይመዋቸዋል፤ እነሱም መጠመቅ፣ መታረም ወይም መሰደድ ናቸው፡፡

መጠመቅ፡- በሚባለው መንገድ ኪራይ ሰብሳቢዎች በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ዶክትሪን ከተሰበኩና ካመኑ በኋላ “የልማታዊ ዜግነት” ጠበል ተረጭተው (ተጠምቀው) ካለፈው ሃጢያታቸው ተሰርየው÷ ምቹ ወንበርና ስልጣን፣ በቂ ደሞዝና ጥቅማጥቅም አግኝተው በሰላም የሚኖሩበት ዕድል ይሰጣቸዋል፡፡ ያለፈው ሃጢያተቸውን ያነሳም “ውሾ ይሁን” ተብሎ ይረገማል፡፡ (በዚህ መንገድ እነ ሽመልስ ከማል፣ እነ ሬድዋን እና እኔ የዚህ ጠመቃ ተጠቃሚዎች ነን፡፡)


መታረም፡- ሁለተኛው ኪራይ ሰብሳቢ የሰይጣን መንፈስን ከዜጎች ውስጥ ለማስወጣት የሚደረግ መፍትሄ ስራይ ሲሆን፤ ኪራይ ሰብሳቢነት የተጠናወተው ግለሰብ በፖሊሶችና በፍርድ ቤት መልካም ፈቃድ በመንግስት ቁጥጥር ስር እንዲሆን ይደረግና ዕውቅ፣ ቻይና አፈራሽ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም፣ አካልን በሚያደክም ስግደት፣ ቁጭ ብድግ፣ በተጨማሪም በተለያዩ ገዳማት እንደሚደረገው በአለንጋ አሳሳች ስጋን በመግረፍ፣ ከዓለምና መረጃ በመገለል ሰይጣኑ እንዲወገድና ታራሚዎቹም “የኢትዮጵያ ሕዝብንና መንግስትን ይቅርታ ጠይቀው” እና ውግዘት ተቀብለው አሊያም ጠቃሚ የምስክርነት መረጃ ሰጥተው እንዲወጡ የሚደረግበት መንገድ ነው፡፡ (በዚህ መንገድ የቅንጅት አመራሮች፣ ብርቱኳን ሚዴቅሳ እና ደበበ እሸቱን የመሳሰሉት “ታርመዋል” ሆነዋል)

መሰደድ፡- የሚባለው መንገድ የላይኞቹ ሁለት መንገዶች ካልተሳኩ የሚመረጠው መንገድ ሲሆን÷ ልማታውያን ኪራይ ሰብሳቢ ሰይጣን የተጠናወታቸው ዜጎች ሰይጣኑን ወደልማታውያን እና መሃል ሰፋሪዎች ከማጋባታቸው በፊት፣ በተለያዩ ጫናዎችና ግፊቶች÷ ሳያስነቁ በሊማሊሞ እንዲያቋርጡ የሚደረግበት መንገድ ነው፡፡ ብዙዎቹ መሰደድን የሚመርጡ ዜጎች ኪራይ ሰብሳቢነቱ የማይለቃቸው ቢሆንም ከሃገር ከወጡ በኋላ በሃገሪቱ ውስጥ ያሉ ዜጎች ላይ ሰይጣኑን ስለማያስተላልፉ፣ በሌላ በኩል ቢሄዱ ቢሄዱ ወዳጅ አገር ወደሆነችው ቻይና ስለማይሄዱ ችግር የለውም፡፡ (በዚህ መንገድ የአዲስ ነገር ጋዜጠኞችን ጨምሮ እነዳዊት ከበደ፣ አበበ ቶላ፣ አርጋው አሽኔ …  እና ወዘተርፈዎች ተጠቅመዋል)

እናም እኔ መጠመቅ የተሰኘው መፍትሄ ስራይ ኤክስቴንሽን ተጠቃሚ ከሆንኩ በኋላ፣ ዓለም በኢኮኖሚ ቀውስ እየታመሰች ባለችበት ጊዜ ሃገራችን ለስምንት ተከታታይ ዓመታት ኢኮኖሚዋ በሁለት ዲጂት እያደገ መምጣቱን ምሳሌ አድርገው ቢንቀሳቀሱ፣ ሌሎችም ሃገራት የፈንጠዝያችን ተጠቃሚ ይሆናሉ የሚል ስሜት ተሰማኝ፡፡ የኢትዮጵያን መልካም ገጽታ ለመቀየር የሚያስችለው በኢኮኖሚ ማደግ ብቻ ሳይሆን ዓለምን በኢኮኖሚ ማሳደግ መሆን እንዳለበት ታውቆኛል፡፡ ምክንያቱም ኢትዮጵያ አድጋ፣ አድጋ እላይ ስትደርስ - ድንበር እየሰበሩ እና ዲቪ እየሞሉ ወደኢትዮጵያ ለመግባት የሚሞክሩት የድሃ ሃገር ሕዝቦች መልሰው ለኛው ሸክም መሆናቸው እንደማይቀር ታይቶኛል፡፡

የኢትዮጵያን ተሞክሮ ለማካፈል ስናስብ ታዲያ÷ “ከባድ ስራ ወስደው፣ ከባድ ስራ በሚሰጡት” ጠቅላይ ሚኒስትራችን ፊት አውራሪነት የሚመራው ፓርላማችን ግንባር ቀደም ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን ነጥቦች የዓለማችን ሃገራት ፓርላማዎች ቢተገብሩ፣ ዕድገታቸው እንደኢትዮጵያ ይሆናል፡፡ ስለዚህ ሁላችሁም አንባብያን ይህንን መልዕክት ‘የሰማህ ላልሰማ አሰማ’ በሚል መርኅ “አምስት ለአንድ በመደራጀት”፣ መረጃውን በማሰራጨት የዓለማችንን ሕዳሴ እናፋጥን!!!

1. አለመጨቃጨቅ፤ ጭቅጭቅ እንኳን ሃገርን ትዳርን የሚያፈርስ ነገር ነው፡፡ ስለዚህ ፓርላማዎች በጠቅላይ ሰብሳቢያቸው የሚቀርበውን ሐሳብ ያለምንም ጭቅጭቅ መቀበል አለባቸው፡፡ የሚጨቃጨቁ ካሉ አፈጉባኤው በዲሲፕሊን ሰበብ ማስቆም ይችላል፣ ጠቅላይ ሰብሳቢው ደግሞ በስድብ መወረፍ አለባቸው፡፡ በዚህ መንገድ ኢትዮጵያ እስከዛሬ ፓርላማ ቀርቦ አንድም ረቂቅ አዋጅ ሳይጸድቅ ያልቀረባት ሃገር በመሆን በዓለም አንደኛ ሆናለች፡፡ የፓርላማ አባላት በሚቀርቡ ሞሽኖችም ላይ ሆነ ረቂቅ አዋጆች ላይ ማቅረብ የሚገባቸው ሙገሳ ብቻ ነው፡፡ ጥያቄ ካላቸው፣ ሊኖራቸው የሚገባው በረቂቅ አዋጁ ፍጽምና ላይ ሳይሆን ዜጎች አዋጁን እንዲቀበሉ ምን ማድረግ ይገባል፣ ኪራይ ሰብሳቢዎች አዋጁን እንዳይቃወሙ እንዴት ዝም ማሰኘት ይቻላል፣ አዋጁ ከጸደቀ በኋላ ዜጎችን እንዴት ማወያየት ይቻላል በሚሉት ተጓዳኝ ጉዳዮች ላይ ብቻ ከሆነ ተቀባይነት ይኖረዋል፡፡

2. እንቅልፍ፤ የፓርላማ አባላት እንቅልፍ የሚወዱ ቢሆን ይመረጣል፡፡ ለአገራቸው ሲሠሩ እያመሹ ቢሆንም ባይሆንም፣ አባላቱ (መጽደቁ በማይቀረው) ረዥም እና ለዛቢስ የረቂቅ አዋጅ ንባብ ተሰላችተው እንቅልፍ ቢያሸልባቸው ችግር የለውም፤ ምክንያቱም ፓርላማ ውስጥ በመተኛቱ ደሞዙ የተቆረጠበት አባል እስካሁን የለም፡፡ ይሄም ሕዝቦች ከዚህ አጋጣሚ በገዛ ጉዳያቸው ላይ መተኛት ምንም ጉዳት እንደማያስከትልባቸው እንዲማሩ ያደርጋል፡፡ ስለዚህ ተቃዋሚ አይኖርም! እንቅልፍ መተኛት፣ ሰውነትን ዘና በማድረግ በስራ ውጤታማ ያደርጋል፤ ይህም በኢትዮጵያ ፓርላማ የተረጋገጠው÷ አሸልበው የነበሩ አባላት በድምጽ ቆጠራ ወቅት እጃቸውን ካላሸለቡት ይልቅ ዘለግ አድርገው ሲያወጡ በመስተዋሉ ነው፡፡

3. መሃይምነት፤ መሃይምነት ለፓርላማ በጣም አስፈላጊ ነገር መሆኑ በአገራችን ተሞክሮ ተረጋግጧል፡፡ የአገራችን አብዛኛው ሕዝብ የትምህርት ዕድል ያልገጠመው በመሆኑ በፓርላማ የሚወክሉት ሕዝቦችም መሃይማን እንዲሆኑ መደረጉ ጠቅሞታል፡፡ ፓርላማው ያለምንም አማራጭ ሐሳብና ውዝግብ፣ በአንድ ዓይነት ሐሳብ መግባባት የቻለው መሃይምነትን በመምረጡ ነው፡፡ የፓርላማ አባላት አንዳንድ የውጭ ቃላትን በመጠቀም የሚነገሩ ንግግሮች የበሰሉ እንደሆኑ ስለሚያምኑ - ጠቅላይ ሰብሳቢው እንግሊዝኛ ቢችሉ ይጠቅማል፡፡ ተቃራኒ ሐሳብ የሚያፈልቁ ሰዎች ቢከሰቱም - ጠቅላይ ሰብሳቢው ቀልድ አዘል ስድብ በመሳደብ፣ መሃይማኑን በማሳቅ ማሳመን ይችላሉ፡፡

እነዚህ ሦስቱ የኢትዮጵያ ፓርላማ ዋነኛ ገጽታ፣ የዕድገታችን ዋልታ በመሆናቸው ሌሎችም ተሞክሮውን ለበጎ ዓላማ እንዲያውሉት በማካፈሌ ኩራት ይሰማኛል፡፡

ግልባጭ፤ ለተባበሩት መንግስታት ዋና ጽ/ቤት

Comments

Popular posts from this blog

The "Corridor Development" is a Façade of the Prosperity Party

Befekadu Hailu I have seen a news report claiming that 40% of central Addis Ababa will be demolished for the corridor development; I am not able to confirm the validity of the news but it sounds real to me given the size of massive operations in the demolition of old neighborhoods and construction of bike lanes, green areas, and glittering street lights. I like to see some beauty added to my city but cannot help mourning the slow death of it too. Addis Ababa was already in a huge crisis of housing and the demolition of houses is exacerbating it. Apparently, Prime Minister Abiy Ahmed is eager to showcase his vision of prosperity by demonstrating how fast his administration can do magic by beautifying the front sides of the streets with lights, new pavements, and painted fences ("to fake it until he makes it" in my friend's words). Therefore, he and his party do not care about the miserable human stories behind the scenes and they will harass you if you tell it (Azeb Woku...

የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ

በፍቃዱ ዘ . ኃይሉ “የአዲስ አበባ ብሔርተኝነት” ቢኖር ኖሮ መሪው ልጅ ሚካኤል ይሆን ነበር። አሁን አሁን እሱ ስለ አዲስ አበባ የዘፈናቸውን ዘፈኖች ቁጥር ራሱ በትክክል መቁጠር ይቸግረኛል። ለአዲስ አበባ ከተዘፈኑ ዘፈኖቹ ውጪም በየዘፈኑ ውስጥ የሚጨማምራቸው መልዕክቶች በራሳቸው መወድሰ አዲስ አበባ ናቸው። ለምሳሌ፣ በቅርቡ በለቀቀው ‘አዲስ አራዳ’ በተሰኘው አልበሙ ውስጥ ‘የድሬ ልጅ’ የሚል ዘፈን አለው። ዘፈኑ የተዘጋጀው ያው የአዲስ አበባ እህት ተደርጋ የምትቆጠረውን ድሬ ዳዋን ለማወደስ ነበር። ልጅ ሚካኤል ግን የአዲስ አበባ ፍቅሩ ያመልጠውና የሚከተለውን ያቀነቅናል፦ “መጣልሽ በሏት፣ ድሬ ድረስ፣  ከአዱ ገነት፣ ከሸገር፣ ከአዲስ ደረሰ፣... የሸገር ልጅ አራዳ ነው፣ ሰው አክባሪ፣ ሰው ወዳዱ፣ ቀላጅና ተረበኛ፣ ፍቅር ይዞ የሚተኛ፣ ‘አለው’ የለ፣ ‘የለው’ የለ፣ ከሁሉ ጋ፣ ግባ ጀባ...፤” ፤ ልጅ ሚካኤል በዚህ አልበሙ ብቻ አዲስ አበባን የሚያውድሰባቸው ሌሎችም ዘፈኖች አሉ፤ ‘ አዲስ አራዳ ’ የሚለው የአልበሙ መጠሪያ እና ‘ሸገር’ የሚሉት ዘፈኖቹ ዋነኞቹ ናቸው። ታዲያ እንዲህ በአዲስ አበባ ፍቅር የሚቃጠለው ልጅ ሚካኤል "ሊነግረን የሚፈልገው ምንድን ነው?" የሚለው ጥያቄ ደጋግሞ ይመጣብኛል። ይህ የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ ምንነትን ለመረዳት የሚጥር ፖለቲካዊ መጣጥፍ ነው። ‘አዲሱ አራዳ’ ማነው? በዚህ ዘፈኑ በብዙዎቻችን ዕድሜ የትዝታ ማኅደር ውስጥ የሚገኙ ነገር ግን በአዲስ አበባ ልማት ሥም የፈረሱ እና እየተረሱ ያሉ ሰፈሮችን ሥም ያነሳሳል። ዘፈኑ በግጥሙም በዜማውም፣ የሐዘን እንጉርጉሮ ያለበት ነው። ምሳሌ እንውሰድ፦ “ጨርሰሽ ስትወጪ ከቡፌ ዳ’ላጋ፣ ጠብቂኝ እንዳልል፣ ቆመሽ መሐሙድ’ጋ፣ አገር ...

መጽሐፍ የሚወጣው፣ የተዋነይ ዘ ጎንጅ 5 መሥመር ቅኔ

ጎንጅ ቅኔ ያጠናበት ደብር ሥም ነው። ደብረ ጥበብ ጎንጅ ቅዱስ ቴዎድሮስ ገዳም። ተዋነይ የባለቅኔው ሥም ነው። (የግዕዝ ትርጉሙ "ዋናተኛ" ማለት ነው።) ሊቁ ተዋነይ የልኅቀቱን ያክል እምብዛም አይወራለትም፤ ነገር ግን በዘመኑ ወደር የሌለው ልኂቅ ስለመሆኑ ሥራው ይናገራል። የሕይወት ተፈራ "Mine to Win" የተሰኘ ድርሰት መቼቱን በዐፄ ዮሓንስ ንግሥና ዘመን፣ በጎጃም/ጎንደር የቅኔ መማሪያ ደብሮች ያደረገ ልብወለድ ነው። ልቦለዱ የቅኔ ትምህርት ስርዓትን ያስተዋውቀናል፤ በበኩሌ የቅኔ ትምህርትን እና የቅኔ ሊቃውንት ታላቅነት ቀድሞ ከነበረኝ ግንዛቤ የበለጠ እንዲሆን አድርጎኛል። በተለይ የተዋነይ ዘ ጎንጅ (በውኑ ዓለም የነበረ ባለቅኔ) ተከታይዋ አምስት መሥመር ቅኔ መጽሐፍ የሚወጣት እንደሆነች ልቦለዱ አሳሰበኝ። ወይም በአጭሩ ብዙ ምዕራባውያን ስንት መጽሐፍ የጻፉለት ፍልስፍናን በአምስት መሥመር ይዟል። የቅኔው ትርጓሜ የመጽሐፍ ቅዱስን እና የመጽሐፍ ቅዱሱን ፈጣሪ ኅልውና ይሞግታል። “የአምን ወይገኒ ኵሉ ዓለም በዘፈጠረ ለሊሁ ብዙኃን እንዘ ይገንዩ ይስግዱ ቅድሜሁ ለነጽሮ ዝኒ ነገር እሥራኤል ከመይፍርሑ ሙሴ ፈጠረ ፈጣሪሁ ወ ፈጣሪ ፈጠረ ኪያሁ።” (ተዋነይ ዘ ጎንጅ። ምንጭ፣ሕይወት ታደሰ ወደአማርኛ የተረጎመችው የሕይወት ተፈራ መጽሐፍ) ትርጉሙን በኋላ እመለስበታለሁ። ስለተዋነይ መጀመሪያ የሰማሁት የበውቀቱ መጽሐፍ ላይ ነበር። እሱም በጨረፍታ - “የሌሊት ዜማዎች” የሚለው ግጥሙ ውስጥ። በውቀቱ ተዋነይን በግጥሙ ግርጌ ማስታወሻው አስተዋውቆን ያልፋል፣ “ተዋነይ በቅኔ ቤት አፈ ታሪክ ሞትን በግዝት ለሰባት ዓመታት ያቆመ ጀግና ነው"። ከዚያ በኋላ፣ አዲስ አድማስ ላይ የወጣ አንድ ጽሑፍ ተዋነይ የተላከበትን ...