Skip to main content

ደጉ ኢትዮጵያዊ፤ ከልብ ካለቀሱ እምባ እንደማይገድ ያስመሰከረ ስብስብ


የዓለም ደቻሳ ልጆች፣ ባለቤት (መሃል) እና ወንድም (በስተቀኝ)
“አለቀለት ሲባል ፍቅር ተሙዋጠጠ
የፌስ ቡክ ዝምድና ነገርን ለወጠ::” ~ Bizu Hiwot
 
“ፌስን ቡክ አድርገው የተቀጣጠሩ
በልብ መነጽር ገጹን ያነበቡ
ሸበሌ ከትመው ታሪክ አስከተቡ፡፡” ~ Desu Aragaw
 
እነዚህ ግጥሞች የተገጠሙት ‹ደጉ ኢትዮጵያዊ› ላዘጋጀው የዓለም ደቻሳ ቤተሰብ ገቢ ማሰባሰቢያ የስነጽሁፍ ምሽት ለተገኘው የመጀመሪያ ስኬት፣ በፌስቡክ ላይ ነው፡፡ ወደስኬቱ በኋላ ላይ የምንመለስበት ቢሆንም መጀመሪያ ‹ደጉ ኢትዮጵያዊ› ምንድን ነው፣ ማነው፣ ከየት ነው፣ ወዴት ነው? የሚሉትን ጥያቄዎች በአጭሩ እንመልስ፡፡
 
‹ደጉ ኢትዮጵያዊ› ከዚህ በፊት በአካል የማይተዋወቁ 16 የፌስቡክ ጓደኛሞች የፈጠሩት የፌስቡክ ቡድን ነው፡፡ የደጉ ሳምራዊን ታሪክ መነሻ አድርጎ÷ በሊባኖስ መንገድ ላይ እየተጎተተች መኪና ውስጥ እንደትገባ ከተደረገች በኋላ በማግስቱ ራሷን አጥፍታለች የተባለችውን ዓለም ደቻሳ ቤተሰቦች የእዝን ለመስጠት እና እግረ መንገዱንም ስለጉዳዩ አሳሳቢነት አነስተኛ ግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም ለማዘጋጀት የተመሰረተው ‹ደጉ ኢትዮጵያዊ› ምንም እንኳን ሕጋዊ ሰውነት የሌለው ቡድን ቢሆንም በበጎ ፈቃደኝነት መስራት የሚፈልጉትን መስራቾቹን እና በፌስቡክ በተከፈተው የቡድኑ ገጽ ውስጥ በገቡ ከ4,000 በላይ አባላቶቹ ድጋፍ የሚከተሉትን ዓላማዎች ግብ አድርጎ ለመንቀሳቀስ ሕልም አለው፡፡
  • የ‹ደጉ ኢትዮጵያ› ቡድን አባላትን ስለቤት ሰራተኞች መብት፣ ጥቃት እና ሌሎችም ነባራዊ ሁኔታዎች መሰረታዊ ግንዛቤ ማስጨበጥ፡፡
  • ከፍተኛ ጥቃት የሚፈፀምባቸውን የቤት ሰራተኛ ተቀባይ ሃገራትን/መዳረሻዎችን ለይቶ ማወቅ እና ማሳወቅ፡፡
  • ትኩረት ወደሚደረግባቸው መዳረሻ ሃገራት በርካታ የቤት ሰራተኞችን ከሚልኩ ወኪሎች (ኤጀንቶች) ጋር ዘላቂ ግንኙነት መፍጠር፡፡
  • ከየትኛው የኢትዮጵያ ክልል በርካታ ሴቶች ለቤት ሰራተኝነት እንደሚሰደዱ ለይቶ በማወቅ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ መስራት፡፡
  • ‹የኢትዮጵያ ማሕበረሰብ› የተባለ የግንኙነት መረብ የቤት ሰራተኛ ተቀባይ በሆኑ መዳረሻ ሃገራት ውስጥ መመስረት እና መሰረታዊ መረጃ እና ድጋፍ መለዋወጥ፡፡
 
‹ደጉ ኢትዮጵያዊ› ትላንት ምን ሠራ?
ደጉ ኢትዮጵያዊ፣ ትላንት ሚያዝያ 11፤ 2004 በዋቢ ሸበሌ ሆቴል አዳራሽ የስነጽሁፍ ምሽት ያዘጋጀ ሲሆን በዝግጅቱ ላይ ወደ 400 የሚጠጉ ሰዎች መገኘታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ገቢው ሙሉ ለሙሉ ለዓለም ደቻሳ ቤተሰቦች በባለቤቷ እና በወንድሟ ስም በተከፈተ አካውንት ገቢ የሚደረግ የመግቢያ ትኬት የተሸጠ ሲሆን፣ ታዳሚዎች እንደየፍላጎታቸው ባለ 25፣ 50 ወይም 100 ብር ትኬት እየገዙ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡ ዋቢሸበሌ ሆቴልን ጨምሮ በርካታ ድርጅቶች እና ግለሰቦች ድጋፋቸውን ያደረጉ በመሆኑ ዝግጅቱን ለማካሄድ ምንም ወጪ አላስፈለገም ማለት ይቻላል፡፡
 
ፕሮግራሙ መጀመሪያ ላይ የሳውንድ ሲስተም መንገራገጭ ከመጋፈጡ በቀር በስኬት ተካሂዷል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ በርካታ አንጋፋ እና አማተር ገጣሚያን ግጥሞቻቸውን ያነበቡ ሲሆን፣ የ10 ደቂቃ ዶኩመንተሪ፣ የደጉ ኢትዮጵያ ቡድን ማስተዋወቂያና አጭር ምክር በአቶ በኃይሉ ገ/መድህን ተደርጓል፡፡ አንዱአለም ተስፋዬም የዳንኤል ክብረትን ጽሁፍ ያነበበ ሲሆን መድረኩን ሜሮን ጌትነት መርታዋለች፡፡ ሙኒት እና ዮርግ ታዳሚውን ለማዝናናት የተገኙ የነበረ ቢሆንም በሳውንድ ሲስተሙ ላይ በተከሰተው ችግር ምክንያት፣ ዮርግ ጊታሩን ባይጫወትም ሙኒት ‹‹አስታውሳለሁ፣ መች እረሳለሁ›› የሚለውን ዜማ በታዳሚው ታጅባ ተጫውታለች፡፡ ከሌሎችም በርካታ የተጋበዙ እንግዶች መካከል የዓለም ደቻሳ ባለቤት፣ ወንድሟ እና ሁለት ልጆቿም እንዲገኙ ተደርጓል፡፡
 
በዕለቱ በር ላይ ከተሸጡት ትኬቶች ብቻ ከ16ሺኅ ብር በላይ የተገኘ ሲሆን÷ ዘግየት ብሎ እንደሰማሁት ደግሞ በፋራናይት ላውንጅ እና ሌሎችም ቦታዎች ተቀምጦ ከነበረ ትኬት የተገኘው ገቢ ሲደማመር ወደ 20,000 ብር ተጠግቷል፡፡ በተጨማሪም አንድ ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ ግለሰብ የልጆቹን ሙሉ የትምህርት ወጪ÷ ትምህርታቸውን እስኪጨርሱ ድረስ ለመሸፈን ቃል ገብተዋል፡፡ ሌሎችም ግለሰቦች የተከፈተውን ባንክ አካውንት ቁጥር የወሰዱ ሲሆን የ‹ደጉ ኢትዮጵያ› ትልቅ ስኬት እንደሆነ የተነገረው ግን በሃገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ በፌስቡክ በተመሰረተ ቡድን አማካይነት ማሕበራዊ ፋይዳ ያለው ሥራ መስራቱና በዚሁ መቀጠል የሚችልበትን ዕድል ለሁሉም ክፍት አድርጎ ማስተዋወቁ ላይ ነው፡፡
------
ከደጉ ኢትዮጵያ ጋር አብሮ ለመሥራት የሚፈልጉ ሰዎች በፌስቡክ ወይም በኢሜይል thegoodethiopian@gmail.com መጻፍ እንደሚችሉ አባላቱ ተናግረዋል፡፡

Comments

  1. Goodn article..and make the correction of the name Andualem Arage....instead Andualem Tesfaye....

    ReplyDelete
  2. ይሄ ቅዱስ እና የተቀደሰ ሃሳብ ነው!! በርቱ ተበራቱ የሚያስብል ነው!!

    ReplyDelete

Post a Comment

Popular posts from this blog

The "Corridor Development" is a Façade of the Prosperity Party

Befekadu Hailu I have seen a news report claiming that 40% of central Addis Ababa will be demolished for the corridor development; I am not able to confirm the validity of the news but it sounds real to me given the size of massive operations in the demolition of old neighborhoods and construction of bike lanes, green areas, and glittering street lights. I like to see some beauty added to my city but cannot help mourning the slow death of it too. Addis Ababa was already in a huge crisis of housing and the demolition of houses is exacerbating it. Apparently, Prime Minister Abiy Ahmed is eager to showcase his vision of prosperity by demonstrating how fast his administration can do magic by beautifying the front sides of the streets with lights, new pavements, and painted fences ("to fake it until he makes it" in my friend's words). Therefore, he and his party do not care about the miserable human stories behind the scenes and they will harass you if you tell it (Azeb Woku...

መጽሐፍ የሚወጣው፣ የተዋነይ ዘ ጎንጅ 5 መሥመር ቅኔ

ጎንጅ ቅኔ ያጠናበት ደብር ሥም ነው። ደብረ ጥበብ ጎንጅ ቅዱስ ቴዎድሮስ ገዳም። ተዋነይ የባለቅኔው ሥም ነው። (የግዕዝ ትርጉሙ "ዋናተኛ" ማለት ነው።) ሊቁ ተዋነይ የልኅቀቱን ያክል እምብዛም አይወራለትም፤ ነገር ግን በዘመኑ ወደር የሌለው ልኂቅ ስለመሆኑ ሥራው ይናገራል። የሕይወት ተፈራ "Mine to Win" የተሰኘ ድርሰት መቼቱን በዐፄ ዮሓንስ ንግሥና ዘመን፣ በጎጃም/ጎንደር የቅኔ መማሪያ ደብሮች ያደረገ ልብወለድ ነው። ልቦለዱ የቅኔ ትምህርት ስርዓትን ያስተዋውቀናል፤ በበኩሌ የቅኔ ትምህርትን እና የቅኔ ሊቃውንት ታላቅነት ቀድሞ ከነበረኝ ግንዛቤ የበለጠ እንዲሆን አድርጎኛል። በተለይ የተዋነይ ዘ ጎንጅ (በውኑ ዓለም የነበረ ባለቅኔ) ተከታይዋ አምስት መሥመር ቅኔ መጽሐፍ የሚወጣት እንደሆነች ልቦለዱ አሳሰበኝ። ወይም በአጭሩ ብዙ ምዕራባውያን ስንት መጽሐፍ የጻፉለት ፍልስፍናን በአምስት መሥመር ይዟል። የቅኔው ትርጓሜ የመጽሐፍ ቅዱስን እና የመጽሐፍ ቅዱሱን ፈጣሪ ኅልውና ይሞግታል። “የአምን ወይገኒ ኵሉ ዓለም በዘፈጠረ ለሊሁ ብዙኃን እንዘ ይገንዩ ይስግዱ ቅድሜሁ ለነጽሮ ዝኒ ነገር እሥራኤል ከመይፍርሑ ሙሴ ፈጠረ ፈጣሪሁ ወ ፈጣሪ ፈጠረ ኪያሁ።” (ተዋነይ ዘ ጎንጅ። ምንጭ፣ሕይወት ታደሰ ወደአማርኛ የተረጎመችው የሕይወት ተፈራ መጽሐፍ) ትርጉሙን በኋላ እመለስበታለሁ። ስለተዋነይ መጀመሪያ የሰማሁት የበውቀቱ መጽሐፍ ላይ ነበር። እሱም በጨረፍታ - “የሌሊት ዜማዎች” የሚለው ግጥሙ ውስጥ። በውቀቱ ተዋነይን በግጥሙ ግርጌ ማስታወሻው አስተዋውቆን ያልፋል፣ “ተዋነይ በቅኔ ቤት አፈ ታሪክ ሞትን በግዝት ለሰባት ዓመታት ያቆመ ጀግና ነው"። ከዚያ በኋላ፣ አዲስ አድማስ ላይ የወጣ አንድ ጽሑፍ ተዋነይ የተላከበትን ...

የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ

በፍቃዱ ዘ . ኃይሉ “የአዲስ አበባ ብሔርተኝነት” ቢኖር ኖሮ መሪው ልጅ ሚካኤል ይሆን ነበር። አሁን አሁን እሱ ስለ አዲስ አበባ የዘፈናቸውን ዘፈኖች ቁጥር ራሱ በትክክል መቁጠር ይቸግረኛል። ለአዲስ አበባ ከተዘፈኑ ዘፈኖቹ ውጪም በየዘፈኑ ውስጥ የሚጨማምራቸው መልዕክቶች በራሳቸው መወድሰ አዲስ አበባ ናቸው። ለምሳሌ፣ በቅርቡ በለቀቀው ‘አዲስ አራዳ’ በተሰኘው አልበሙ ውስጥ ‘የድሬ ልጅ’ የሚል ዘፈን አለው። ዘፈኑ የተዘጋጀው ያው የአዲስ አበባ እህት ተደርጋ የምትቆጠረውን ድሬ ዳዋን ለማወደስ ነበር። ልጅ ሚካኤል ግን የአዲስ አበባ ፍቅሩ ያመልጠውና የሚከተለውን ያቀነቅናል፦ “መጣልሽ በሏት፣ ድሬ ድረስ፣  ከአዱ ገነት፣ ከሸገር፣ ከአዲስ ደረሰ፣... የሸገር ልጅ አራዳ ነው፣ ሰው አክባሪ፣ ሰው ወዳዱ፣ ቀላጅና ተረበኛ፣ ፍቅር ይዞ የሚተኛ፣ ‘አለው’ የለ፣ ‘የለው’ የለ፣ ከሁሉ ጋ፣ ግባ ጀባ...፤” ፤ ልጅ ሚካኤል በዚህ አልበሙ ብቻ አዲስ አበባን የሚያውድሰባቸው ሌሎችም ዘፈኖች አሉ፤ ‘ አዲስ አራዳ ’ የሚለው የአልበሙ መጠሪያ እና ‘ሸገር’ የሚሉት ዘፈኖቹ ዋነኞቹ ናቸው። ታዲያ እንዲህ በአዲስ አበባ ፍቅር የሚቃጠለው ልጅ ሚካኤል "ሊነግረን የሚፈልገው ምንድን ነው?" የሚለው ጥያቄ ደጋግሞ ይመጣብኛል። ይህ የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ ምንነትን ለመረዳት የሚጥር ፖለቲካዊ መጣጥፍ ነው። ‘አዲሱ አራዳ’ ማነው? በዚህ ዘፈኑ በብዙዎቻችን ዕድሜ የትዝታ ማኅደር ውስጥ የሚገኙ ነገር ግን በአዲስ አበባ ልማት ሥም የፈረሱ እና እየተረሱ ያሉ ሰፈሮችን ሥም ያነሳሳል። ዘፈኑ በግጥሙም በዜማውም፣ የሐዘን እንጉርጉሮ ያለበት ነው። ምሳሌ እንውሰድ፦ “ጨርሰሽ ስትወጪ ከቡፌ ዳ’ላጋ፣ ጠብቂኝ እንዳልል፣ ቆመሽ መሐሙድ’ጋ፣ አገር ...