Skip to main content

የቴዲ አፍሮን አልበም ያልገዛሁባቸው 5 ምክንያቶች


ባለፈው ሳምንት የቴዲ አፍሮን አልበም እንድንገዛ የሚያስገድዱንን 5 ምክንያቶች አንብቤ ነበር፤ አላሳመኑኝም እንጂ! ስለዚህ አልገዛሁም፡፡ ባልገዛም አዳምጬዋለሁ፡፡ በርግጥ ሳይወጣ በፊት ላለመግዛት መወሰኔ በራሱ፣ ከወጣ በኋላ ለምን አልገዛሁትም ብዬ የምናገረው ነገር ሰሚን ላይማርክ ይችላል ግን ምንአገባኝ፡፡ ግን ምናልባት ‹ገንዘብ ቸግሮት የቴዲን አልበም አልገዛም› ብለው የሚያሙኝን ሰዎች ዝም ለማሰኘት ምክንያቴን እደረድራለሁ፡፡ (በነገራችን ላይ ትላንት ከኢትዮፒካሊንክ እንደሰማሁት÷ ያቺ እንኳን የፕሬዚደንት ግርማ ወልደጊዮርገስን የሕይወት ታሪክ በዶኩመንተሪ እሰራለሁ ስትል የነበረችው አምለሰት ሙጪ ስንት ሳዱላዎች የተጋደሉለትን ቴዲን በእጇ አደረገችው ማለት ነው በቃ?)
5. የአማርኛ አልበም መሆኑን አላወቅኩም ነበር
አልበሙ የአማርኛ መሆኑን ያወቅኩት ከሰማሁት በኋላ ነው፡፡ ምክንያቱም በየቦታው የተለጣጠፉት ግባብዲያ ማስታወቂያዎች በሙሉ ‹Tikur Sew, Get ready, A feast for soul, Teddy Afro ምናምን ይሉና፤ ለሳቅ ለጫወታ ማን እንደ ሜታ!› ይላሉ፡፡ እኔ የመሰለኝ ታዲያ ‹ትኩር ሰው› የሚባል የእንግሊዝኛን አልበም በኢትዮጵያዊ ቢራ አጣጥሙ የተባለ ነበር፤ እንግሊዝኛ እውቀቴ ውሱን ስለሆነ ያገሬን ዘለሰኛ ብሰማ ይሻለኛል ብዬ ነበር፡፡ እሺ! ቀልዴን ነው፡፡ የእንግሊዝኛ አልመሰለኝም፤ ነገር ግን ራሱን እንደኢትዮጵያዊ አርአያነት የሚቆጥረው ቴዲ አልበም ማስታወቂያ በእንግሊዝኛ ብቻ ሲሰራ ማኔጀሩ እና ፕሮሞተሩ አገሩ ኢትዮጵያ እንደሆነ ቢጠፋቸው እንኳን እሱን አላማከሩትም ነበር? አላምንም!

4. የነጠላ ዜማዎቹ ግጥምና ዜማ originality ስላነሳቸው
የቴዲ አፍሮ ዘፈኖች በግጥምም፣ በዜማም ስሜት ይኮረኩሩ እንደነበር የታወቀ ነው፡፡ ሆኖም ባሁኑ ሲለቃቸው የነበሩት ዜማዎች አንዴ ከኤርትራ፣ አንዴ ከሩቅ ምናምን የተቀነጫጨቡ መሆናቸውን ስንሰማ ታዝበናል፡፡ አንድ ግጥሙም ከማኅልዬ ማኅልዬ ዘ ሰለሞን ቃላቶች የተገጣጠሙ መሆናቸው አደናግሮኝ ነበር፡፡ እንዲያውም አንድ ጓደኛዬ ‹‹በቃ ቴዲ የሚችለው ግጥም ነው፤ ዜማ ከየትም፣ ከየትም ትንሽ እየቀባባ…›› ያለውን ለማመን ተቃርቤያለሁ፡፡ የሚያሳዝነው ግን አልበሙን ካደመጥኩ በኋላ ‹ያ አስደናቂው፣ አወዛጋቢው፣ አዲስ ምልከታ አጫሪው የቴዲ አፍሮ የግጥም ችሎታ የት ገባ?› አሰኝቶኛል፡፡

3. አልበሙ ስለወረደብኝ!
እዚህችጋ የቴዲ አድናቂ ብቻ ለመሆን የተፈጠሩ የሚመስሉት አድናቂዎቹ÷ የቴዲ ዘፈኖች አድማጭ ያስፈልገዋል ሊሉኝ ይችላሉ፡፡ ዘፈኖቹን ሦስት፣ አራቴ ሰማሁዋቸው፡፡ ተመልሶ ችክ ባሉ ችክችካዎች ሊያተክረን መሆኑን ሳስበው አሳዘነኝ፡፡ አልበሙን አውሶ ያስቀዳኝ ጓደኛዬም ቴዲን ከጠበቅኩበት በታች ሳገኘው ‹‹ሆዴ ባባ፣ ተናነቀኝ እምባ›› እንጂ አላነደደኝም አለኝ፡፡ ምናልባት ኃይል የሚለው ዘፈን ላይ ያለው ከኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን የተወሰደ ዜማ በሬጌ ስልት ሲሰማ የሚሰጠው ጣዕም ወጣ ያለና የሚያረካ ሊባል ይችል ይሆናል፡፡ ከዚያ በተረፈ እነ ጃ ያስተሰርያልን፣ እነ ካብ ዳኅላክን፣ እነ ሼመንደፈርን በሰማሁበት ጆሮዬ እና እሱም በዘፈነበት አፉ አሁን የዘፈናቸው ለኛም ከሚገባን በታች፣ ለእርሱም ከሚችለው በላይ ሳይሆን አይቀርም፤ ትንሽ ይደብራል፡፡

2. ውድ ነው፤ (ዋጋው!)
30 ብር ለአንድ አልበም?! በዚህ ዘመን ቴክኖሎጂ፣ በአምስት መቶ ሺኅ ቅጂዎች የሚዘጋጅ አንድ ሲዲ ከነሽፋን ማሸጊያው ጭምር የሚፈጀው ዋጋ 5 ብር አይሞላም፡፡ ታዲያ የእርሱ አልበም ምን ስለሆነ ነው 30 ብር የሚሸጠው? በየትኛውም ቴክኖሎጂ ቢሰራ ኮፒ ማድረግ እንደሚቻል ስለማውቅ፣ ኮፒ አድርጌ ተጠቅሜያለሁ፡፡ በበኩሌ አልበሙ 11 ዘፈኖች ስላሉት፣ በ11 ብር ቢሸጥ ኖሮ የመጀመሪያውን (original) ቅጂ እገዛ ነበር፡፡ ይህችኛዋ አመፃ በቴዲ ላይ ብቻ ሳይሆን በሁሉም አርቲስቶች ላይ ነው - አዎ! ኦሪጅናል የሚባለውን አልገዛም፡፡ ምክንያቱም ተመሳሳይ ጥራት ያለውን ቅጂ፣ በነፃ ወይም ግፋ ቢል በ5 ብር አገኛለሁ፡፡ አሥር ብር የምትሸጡ ከሆነ ‹‹ለጥበቡ እድገት›› ስል እተባበራችኋለሁ፡፡

1. ይህንን መንግስት እና ይህንን ኑሮ አላማረረም (I don’t want art for the sake of art)
‹እንዴ ቴዲ እኮ ዘፋኝ ነው?› ካላችሁ፣ እንዴ እስክንድርም እኮ ጋዜጠኛ ነው እላችኋለሁ፤ ‹እንዴ ቴዲን እኮ እያሰሩት ነው?› ካላችሁ፣ እንዴ እስክንድርንም እኮ ከሰባቴ በላይ አስረውታል እላችኋለሁ፡፡ ‹የፈለገውን አቋም መያዝ፣ ማራመድ ወይም አለማራመድ አይችልም እንዴ?› ካላችሁ ግን እስማማለሁ ግን ባያስጀምረን ነበር፡፡ የምርጫ 97 ሰሞን ጥዑም ፖለቲካ ዘፍኖ ከዘፋኝነት ወደነፃ አውጪነት ካሸጋገርነው በኋላ ማፈግፈጉ ያኔ የሕዝቡን ትኩሳት ተንተርሶ ሊጠቀምብን ነበር ማለት ነው? ያኔ ተቃዋሚዎች ተስፋ አላቸው ከነርሱ ልወዳጅ ብሎ ነበር ማለት ነው? ዛሬ ድንገት ተነስቶ ‹የለም! ኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ ያለውን ነገር አላየሁም፣ አልሰማሁም› ቢል እኔም አልሰማውም፡፡  

Comments

  1. we love it we have it take your garbage coment to weyane tv that the only placeu shit.

    ReplyDelete
  2. አረ Anonymous ምን ዓይነት አስተያየት ነው፡፡ የቴዲ አድናቂ ለመሆን፤ ባለጌ መሆን የሚያስፈልግ አስመሰልከ/ሺ/ው እኮ፡፡ ቴዲ ስለ ግብረገብ አልዘፈነም እንዴ!

    ReplyDelete
  3. እኚህ አስተያየቶች ለቴዲ ያለንን ፍቅር ከሙያ አንጻር የሚገመግም ስለሆነ ወድጄዋለሁ!! በሙያ አንጻር እና በገበያ አንጻር ከታየ እውነትም 30 ብር ለአንድ አልበም ውድ ነው!! እንግዲህ ቴዲ እሰከዛሬ የሰራቸውን አልበሞች እናውቃቸዋለን!! ሁሌም ቢደመጡ ቶሎ የሚሰለቹ አይደሉም ከዚህኛው ስራው ጋር ሲነጻጸር!!ሌላው ደሞ ከገበያ አንጻር በዚህ የኑሮ ውድነት የትም በየካፌው እና በየታክሲው የሚደመጥ ስለሆነ 30 ብር ማውጣት ምክንያት ላይሆን ይችላል!! ነገር ግን ለቴዲ ያለውን ፍቅር ብናየው አብዛኛው የኢትዮጰያ ህዝብ ኤርትራውያንንም ጨምሮ ልዩ ፍቅር አለን!! ሁሉንም ላያካትት ይችላል ግን አብዛኛው ብል ማጋነን አይሆንም ስለሚወደድ ብቻ ምንም ይዝፈን ምንም አ ብሎ ማዳመጥ ትንሽ ይከብዳል!! አስተያየት ቢሰጥበት ደሞ ቀጣይ አልበሙ በደምብ እንዲወደድ ስለሚፈልግ የጠነከረ ፍትጊያ እንደሚጠብቀው ቢያውቅ የተሻለ ስራ ይዞ እንዲመጣ ያበረታታዋል ስለዚህ ጥሩ አስተያየት ነው ወድጄዋለሁ!!!

    ReplyDelete
  4. Tedy's songs are amazing; the more I listen the more I like them. Amazing singer. We love you Tedy!

    ReplyDelete
  5. ዕይታህን በጣም አድንቄልሃለው።

    ReplyDelete

Post a Comment

Popular posts from this blog

The "Corridor Development" is a Façade of the Prosperity Party

Befekadu Hailu I have seen a news report claiming that 40% of central Addis Ababa will be demolished for the corridor development; I am not able to confirm the validity of the news but it sounds real to me given the size of massive operations in the demolition of old neighborhoods and construction of bike lanes, green areas, and glittering street lights. I like to see some beauty added to my city but cannot help mourning the slow death of it too. Addis Ababa was already in a huge crisis of housing and the demolition of houses is exacerbating it. Apparently, Prime Minister Abiy Ahmed is eager to showcase his vision of prosperity by demonstrating how fast his administration can do magic by beautifying the front sides of the streets with lights, new pavements, and painted fences ("to fake it until he makes it" in my friend's words). Therefore, he and his party do not care about the miserable human stories behind the scenes and they will harass you if you tell it (Azeb Woku...

መጽሐፍ የሚወጣው፣ የተዋነይ ዘ ጎንጅ 5 መሥመር ቅኔ

ጎንጅ ቅኔ ያጠናበት ደብር ሥም ነው። ደብረ ጥበብ ጎንጅ ቅዱስ ቴዎድሮስ ገዳም። ተዋነይ የባለቅኔው ሥም ነው። (የግዕዝ ትርጉሙ "ዋናተኛ" ማለት ነው።) ሊቁ ተዋነይ የልኅቀቱን ያክል እምብዛም አይወራለትም፤ ነገር ግን በዘመኑ ወደር የሌለው ልኂቅ ስለመሆኑ ሥራው ይናገራል። የሕይወት ተፈራ "Mine to Win" የተሰኘ ድርሰት መቼቱን በዐፄ ዮሓንስ ንግሥና ዘመን፣ በጎጃም/ጎንደር የቅኔ መማሪያ ደብሮች ያደረገ ልብወለድ ነው። ልቦለዱ የቅኔ ትምህርት ስርዓትን ያስተዋውቀናል፤ በበኩሌ የቅኔ ትምህርትን እና የቅኔ ሊቃውንት ታላቅነት ቀድሞ ከነበረኝ ግንዛቤ የበለጠ እንዲሆን አድርጎኛል። በተለይ የተዋነይ ዘ ጎንጅ (በውኑ ዓለም የነበረ ባለቅኔ) ተከታይዋ አምስት መሥመር ቅኔ መጽሐፍ የሚወጣት እንደሆነች ልቦለዱ አሳሰበኝ። ወይም በአጭሩ ብዙ ምዕራባውያን ስንት መጽሐፍ የጻፉለት ፍልስፍናን በአምስት መሥመር ይዟል። የቅኔው ትርጓሜ የመጽሐፍ ቅዱስን እና የመጽሐፍ ቅዱሱን ፈጣሪ ኅልውና ይሞግታል። “የአምን ወይገኒ ኵሉ ዓለም በዘፈጠረ ለሊሁ ብዙኃን እንዘ ይገንዩ ይስግዱ ቅድሜሁ ለነጽሮ ዝኒ ነገር እሥራኤል ከመይፍርሑ ሙሴ ፈጠረ ፈጣሪሁ ወ ፈጣሪ ፈጠረ ኪያሁ።” (ተዋነይ ዘ ጎንጅ። ምንጭ፣ሕይወት ታደሰ ወደአማርኛ የተረጎመችው የሕይወት ተፈራ መጽሐፍ) ትርጉሙን በኋላ እመለስበታለሁ። ስለተዋነይ መጀመሪያ የሰማሁት የበውቀቱ መጽሐፍ ላይ ነበር። እሱም በጨረፍታ - “የሌሊት ዜማዎች” የሚለው ግጥሙ ውስጥ። በውቀቱ ተዋነይን በግጥሙ ግርጌ ማስታወሻው አስተዋውቆን ያልፋል፣ “ተዋነይ በቅኔ ቤት አፈ ታሪክ ሞትን በግዝት ለሰባት ዓመታት ያቆመ ጀግና ነው"። ከዚያ በኋላ፣ አዲስ አድማስ ላይ የወጣ አንድ ጽሑፍ ተዋነይ የተላከበትን ...

የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ

በፍቃዱ ዘ . ኃይሉ “የአዲስ አበባ ብሔርተኝነት” ቢኖር ኖሮ መሪው ልጅ ሚካኤል ይሆን ነበር። አሁን አሁን እሱ ስለ አዲስ አበባ የዘፈናቸውን ዘፈኖች ቁጥር ራሱ በትክክል መቁጠር ይቸግረኛል። ለአዲስ አበባ ከተዘፈኑ ዘፈኖቹ ውጪም በየዘፈኑ ውስጥ የሚጨማምራቸው መልዕክቶች በራሳቸው መወድሰ አዲስ አበባ ናቸው። ለምሳሌ፣ በቅርቡ በለቀቀው ‘አዲስ አራዳ’ በተሰኘው አልበሙ ውስጥ ‘የድሬ ልጅ’ የሚል ዘፈን አለው። ዘፈኑ የተዘጋጀው ያው የአዲስ አበባ እህት ተደርጋ የምትቆጠረውን ድሬ ዳዋን ለማወደስ ነበር። ልጅ ሚካኤል ግን የአዲስ አበባ ፍቅሩ ያመልጠውና የሚከተለውን ያቀነቅናል፦ “መጣልሽ በሏት፣ ድሬ ድረስ፣  ከአዱ ገነት፣ ከሸገር፣ ከአዲስ ደረሰ፣... የሸገር ልጅ አራዳ ነው፣ ሰው አክባሪ፣ ሰው ወዳዱ፣ ቀላጅና ተረበኛ፣ ፍቅር ይዞ የሚተኛ፣ ‘አለው’ የለ፣ ‘የለው’ የለ፣ ከሁሉ ጋ፣ ግባ ጀባ...፤” ፤ ልጅ ሚካኤል በዚህ አልበሙ ብቻ አዲስ አበባን የሚያውድሰባቸው ሌሎችም ዘፈኖች አሉ፤ ‘ አዲስ አራዳ ’ የሚለው የአልበሙ መጠሪያ እና ‘ሸገር’ የሚሉት ዘፈኖቹ ዋነኞቹ ናቸው። ታዲያ እንዲህ በአዲስ አበባ ፍቅር የሚቃጠለው ልጅ ሚካኤል "ሊነግረን የሚፈልገው ምንድን ነው?" የሚለው ጥያቄ ደጋግሞ ይመጣብኛል። ይህ የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ ምንነትን ለመረዳት የሚጥር ፖለቲካዊ መጣጥፍ ነው። ‘አዲሱ አራዳ’ ማነው? በዚህ ዘፈኑ በብዙዎቻችን ዕድሜ የትዝታ ማኅደር ውስጥ የሚገኙ ነገር ግን በአዲስ አበባ ልማት ሥም የፈረሱ እና እየተረሱ ያሉ ሰፈሮችን ሥም ያነሳሳል። ዘፈኑ በግጥሙም በዜማውም፣ የሐዘን እንጉርጉሮ ያለበት ነው። ምሳሌ እንውሰድ፦ “ጨርሰሽ ስትወጪ ከቡፌ ዳ’ላጋ፣ ጠብቂኝ እንዳልል፣ ቆመሽ መሐሙድ’ጋ፣ አገር ...