Skip to main content

ከአከሌን አሰሩት እስከ አከሌን አገዱት!


ሰሞኑን ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ የተሰኘ እና መቀመጫውን ሰሜን አሜሪካ ያደረገ ቡድን ባጋለጠው መረጃ መሰረት INSA (Infromation Network Security Agency) በመባል የሚታወቀው መንግስታዊ ድርጅት ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር የ‹‹ተጠርጣሪ›› ግለሰቦችን ንግግር በመጥለፍ ሲያዳምጥ እና ሲቀዳ ይውላል ይለናል፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ምን እንደተከሰተ ባይታወቅም ይኸው INSA ከዚህ በፊት ከነበረው ትጋት በበለጠ በአንድ ሳምንት ብቻ ከመቶ በላይ ድረአምባዎችን እና ጦማሮችን አግዷል፡፡

የጦማር እገዳው ዘመቻ ጠንካራ ከመሆኑ የተነሳ አንዳንድ ጦማሪዎች ሲዘጋባቸው፣ አዲስ ሲከፍቱ፤ ሲዘጋባቸው፣ አዲስ ሲከፍቱ ሰንብተዋል፡፡ በፖለቲካዊ ሽሙጦቹ መንግስትን የሚያንጰረጵረው አቤ ቶክቻው (ይህንን ጽሁፍ እስከጻፍኩበት ጊዜ ድረስ ብቻ) ሰባት ጦማሮችን በመክፈት ክብረወሰን ለመስበር በቅቷል፡፡


INSA በድረአምባው ላይ በእንግሊዝኛ ያሰፈረው ተልዕኮው ‹በምርምር ላይ ተመስርተው በሚዘጋጁ መተግበሪያዎች የመንግስትንና የሕዝብን የመረጃ ስርዐቶች በብቃት ከአደጋ መጠበቅ የሚያስችል አቅም መገንባት፤› እንደሆነ ይናገራል፡፡ በራዕዩ፣ ዓላማዎቹ እና አገልግሎቶቹ ዝርዝር ውስጥ መረጃዎችን እና ድረአምባዎችን ማገድ የሚል ነገር ፈልጌ አላገኘሁም፡፡ እኔም በበኩሌ ከላይ ባስነበብኳችሁ ተልዕኮው መሠረት INSA በቫይረስ፣ በሃከሮች ወይም በሌሎች የደህንነት ስጋቶች የሚሰነዘርብኝን ጥቃት ይከላከልልኛል ብዬ ሳስብ፣ በተቃራኒው ጦማሬን በማገድ አስደንግጦኛል፡፡ እንደሕግ አክባሪ ዜግነቴ የምገፈግፈው ታክስ እኔኑ ለማፈን መልሶ መዋሉ እጅግ አሳፋሪ ነው፡፡

OpenNet Initiative (ONI) የተሰኘ ድምበር የለሽ ተቋም በየሃገራቱ የሚታገዱ ድረአምባዎችን ሁኔታ እና ምክንያቶች በየዓመቱ የመተንተን ስራ ይሰራል፡፡ OpenNet በማገድ ተግባራቸው ሃገራትን Pervasive Substantial Selective Suspected No evidence እያለ ከጭፍን አጋጆች እስከ ነፃ የሚባሉትን ይመድባል፡፡ በዚህ ምድቡ፣ ያውም የዚህ ሳምንቱ ጉድ ከመሰማቱ በፊት ባወጣው ሪፖርት ኢትዮጵያን Substantial የተባለው ምድብ ውስጥ አስቀምጧታል፡፡

ኢትዮጵያ የነበረችበት ምድብ (የነበረችበት የምለው በዚህ ሰሞን አካሄዷ Pervasive የተሰኘውን እና ተቃራኒ ሐሳብ ለማንሳት የሚዳዳቸውን ሁሉ ከማገድ የማይመለሱት ምድብ ውስጥ ትቀላቀላለች የሚል እምነት ስላለኝ ነው፤) እናም በነበረችበት ምድብ ውስጥ በተወሰነ የፖለቲካ ርዕስ ብቻ ሳይሆን በሌሎች በርካታ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ የሚጽፉ ድረአምባዎች ወይም ጦማሮችም እንደሚታገዱ OpenNet ይናገራል፡፡

ሕገ መንግስቱን እናስታውሳቸው!
መንግስት ካወጣው በኋላ የዘነጋውን ሕገመንግስት እንከን አልባ እንደሆ ይዘምርለታል፡፡ እኛ ግን አማራጭ የለንምና ከነእንከኑም ቢሆን እየተገዛንለት እንገኛለን፡፡

የሕገመንግስቱ አንቀጽ 29/2 ‹ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት ሐሳቡን የመግለጽ ነጻነት አለው፡፡ ይህ ነጻነት በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ወሰን ሳይደረግበት በቃልም ሆነ በጽሑፍ ወይም በሕትመት፣ በስነጥበብ መልክ ወይም በመረጠው በማንኛውም የማሰራጫ ዘዴ፣ ማንኛውንም ዓይነት መረጃና ሐሳብ የመሰብሰብ፣ የመቀበልና የማሰራጨት ነጻነቶችን ያካትታል› ይላል፡፡

ይኸው ሕገ መንግስት ‹የቅድሚያ ምርመራ በማንኛውም መልኩ የተከለከለ መሆኑን፣› እና ሕዝብ ‹ጥቅሙን የሚመለከት መረጃ የማግኘት ዕድል› እንዳለው ያስቀምጣል፡፡

እነዚህ መብቶች ከወረቀት ወደመሬት ወርደው ማየት የኢትዮጵያ ሕዝብ የዘወትር ምኞት ነው፡፡ ምክንያቱም እውነታው፡-
  • የመንግስትን ሥራ የሚናገሩ (ወይም ከውዳሴ በቀር ሌላ ጉዳይ /ለምሳሌ ድክመቱን እና ስህተቱን/ ስለመንግስት የሚያወሩ ወይም ከገዢው ፓርቲ ውጪ ሕዝቡ አማራጭ እንዳለው የሚጠቁሙ) ግለሰቦች እና የዜና ምንጮች ይታሰራሉ፣ ይታገዳሉ፡፡
  • አሁን ደግሞ፣ በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት አዲሱ የሕትመት ሥራ ውል ላይ ማተሚያ ቤቱ አሳታሚዎቹ ለሚያወጡት ጽሁፍ ይዘት በሕግ ተጠያቂ አይሆንም ካለ በኋላ፤ ለሕትመት የሚቀርብለት ጽሁፍ ሕግን እንደሚጥስ በቂ ማስረጃ ካለው አላትምም የማለት መብት አለው እያለ ነው፡፡ ማለት ‹‹የተከለከለውን›› ቅድመ ምርመራ አድርጎ ሲያበቃ ማለት ነው! (አንቀጽ 9 እና 10)

ዴሞክራሲ በሒደት እንደሚያድግ የኢሕአዴግ ባለስልጣናት አበክረው እየነገሩን ነው፡፡ በርግጥ እኔም በአባባሉ እስማማለሁ፡፡ ነገር ግን ዴሞክራሲ በሒደት አያሽቆለቁልም፡፡ መረጃ የማግኘትን እና የመስጠትን ነጻነትን ከመቀማት የበለጠ የዴሞክራሲ ማሽቆልቆል ሊመጣ አይችልም፡፡ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ተስፋ ከጊዜ ወደጊዜ እየተሟጠጠ ወርዶ አሁን ስሙ ራሱ በቴሌቪዥን ከተነሳ ከርሟል፡፡

ነገር ግን አሁንም እንዲህ እላለሁ፤ በዴሞክራሲ ተስፋ ያልቆረጣችሁ፣ ነጻነታችሁን አሳልፋችሁ ላለመስጠት የቆረጣችሁ ጦማሪ ወዳጆቼ ሆይ - ከ‹አንድ ብርቱ› ነውና ተረቱ - ኑ መንግስትን እንክሰሰው!!!

Comments

  1. Yes my taxpayer money is filling these chinese hackers pocket.shame on our rulers who ones said they were fighting to remove mercyless dictator.and for that couse thousend and thousends lives had been sacrificed.After all that you preach us to choose bread than democracy.HELLO we didn't still find thd bread on the table three times a day after 20 years.

    ReplyDelete

Post a Comment

Popular posts from this blog

The "Corridor Development" is a Façade of the Prosperity Party

Befekadu Hailu I have seen a news report claiming that 40% of central Addis Ababa will be demolished for the corridor development; I am not able to confirm the validity of the news but it sounds real to me given the size of massive operations in the demolition of old neighborhoods and construction of bike lanes, green areas, and glittering street lights. I like to see some beauty added to my city but cannot help mourning the slow death of it too. Addis Ababa was already in a huge crisis of housing and the demolition of houses is exacerbating it. Apparently, Prime Minister Abiy Ahmed is eager to showcase his vision of prosperity by demonstrating how fast his administration can do magic by beautifying the front sides of the streets with lights, new pavements, and painted fences ("to fake it until he makes it" in my friend's words). Therefore, he and his party do not care about the miserable human stories behind the scenes and they will harass you if you tell it (Azeb Woku...

መጽሐፍ የሚወጣው፣ የተዋነይ ዘ ጎንጅ 5 መሥመር ቅኔ

ጎንጅ ቅኔ ያጠናበት ደብር ሥም ነው። ደብረ ጥበብ ጎንጅ ቅዱስ ቴዎድሮስ ገዳም። ተዋነይ የባለቅኔው ሥም ነው። (የግዕዝ ትርጉሙ "ዋናተኛ" ማለት ነው።) ሊቁ ተዋነይ የልኅቀቱን ያክል እምብዛም አይወራለትም፤ ነገር ግን በዘመኑ ወደር የሌለው ልኂቅ ስለመሆኑ ሥራው ይናገራል። የሕይወት ተፈራ "Mine to Win" የተሰኘ ድርሰት መቼቱን በዐፄ ዮሓንስ ንግሥና ዘመን፣ በጎጃም/ጎንደር የቅኔ መማሪያ ደብሮች ያደረገ ልብወለድ ነው። ልቦለዱ የቅኔ ትምህርት ስርዓትን ያስተዋውቀናል፤ በበኩሌ የቅኔ ትምህርትን እና የቅኔ ሊቃውንት ታላቅነት ቀድሞ ከነበረኝ ግንዛቤ የበለጠ እንዲሆን አድርጎኛል። በተለይ የተዋነይ ዘ ጎንጅ (በውኑ ዓለም የነበረ ባለቅኔ) ተከታይዋ አምስት መሥመር ቅኔ መጽሐፍ የሚወጣት እንደሆነች ልቦለዱ አሳሰበኝ። ወይም በአጭሩ ብዙ ምዕራባውያን ስንት መጽሐፍ የጻፉለት ፍልስፍናን በአምስት መሥመር ይዟል። የቅኔው ትርጓሜ የመጽሐፍ ቅዱስን እና የመጽሐፍ ቅዱሱን ፈጣሪ ኅልውና ይሞግታል። “የአምን ወይገኒ ኵሉ ዓለም በዘፈጠረ ለሊሁ ብዙኃን እንዘ ይገንዩ ይስግዱ ቅድሜሁ ለነጽሮ ዝኒ ነገር እሥራኤል ከመይፍርሑ ሙሴ ፈጠረ ፈጣሪሁ ወ ፈጣሪ ፈጠረ ኪያሁ።” (ተዋነይ ዘ ጎንጅ። ምንጭ፣ሕይወት ታደሰ ወደአማርኛ የተረጎመችው የሕይወት ተፈራ መጽሐፍ) ትርጉሙን በኋላ እመለስበታለሁ። ስለተዋነይ መጀመሪያ የሰማሁት የበውቀቱ መጽሐፍ ላይ ነበር። እሱም በጨረፍታ - “የሌሊት ዜማዎች” የሚለው ግጥሙ ውስጥ። በውቀቱ ተዋነይን በግጥሙ ግርጌ ማስታወሻው አስተዋውቆን ያልፋል፣ “ተዋነይ በቅኔ ቤት አፈ ታሪክ ሞትን በግዝት ለሰባት ዓመታት ያቆመ ጀግና ነው"። ከዚያ በኋላ፣ አዲስ አድማስ ላይ የወጣ አንድ ጽሑፍ ተዋነይ የተላከበትን ...

የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ

በፍቃዱ ዘ . ኃይሉ “የአዲስ አበባ ብሔርተኝነት” ቢኖር ኖሮ መሪው ልጅ ሚካኤል ይሆን ነበር። አሁን አሁን እሱ ስለ አዲስ አበባ የዘፈናቸውን ዘፈኖች ቁጥር ራሱ በትክክል መቁጠር ይቸግረኛል። ለአዲስ አበባ ከተዘፈኑ ዘፈኖቹ ውጪም በየዘፈኑ ውስጥ የሚጨማምራቸው መልዕክቶች በራሳቸው መወድሰ አዲስ አበባ ናቸው። ለምሳሌ፣ በቅርቡ በለቀቀው ‘አዲስ አራዳ’ በተሰኘው አልበሙ ውስጥ ‘የድሬ ልጅ’ የሚል ዘፈን አለው። ዘፈኑ የተዘጋጀው ያው የአዲስ አበባ እህት ተደርጋ የምትቆጠረውን ድሬ ዳዋን ለማወደስ ነበር። ልጅ ሚካኤል ግን የአዲስ አበባ ፍቅሩ ያመልጠውና የሚከተለውን ያቀነቅናል፦ “መጣልሽ በሏት፣ ድሬ ድረስ፣  ከአዱ ገነት፣ ከሸገር፣ ከአዲስ ደረሰ፣... የሸገር ልጅ አራዳ ነው፣ ሰው አክባሪ፣ ሰው ወዳዱ፣ ቀላጅና ተረበኛ፣ ፍቅር ይዞ የሚተኛ፣ ‘አለው’ የለ፣ ‘የለው’ የለ፣ ከሁሉ ጋ፣ ግባ ጀባ...፤” ፤ ልጅ ሚካኤል በዚህ አልበሙ ብቻ አዲስ አበባን የሚያውድሰባቸው ሌሎችም ዘፈኖች አሉ፤ ‘ አዲስ አራዳ ’ የሚለው የአልበሙ መጠሪያ እና ‘ሸገር’ የሚሉት ዘፈኖቹ ዋነኞቹ ናቸው። ታዲያ እንዲህ በአዲስ አበባ ፍቅር የሚቃጠለው ልጅ ሚካኤል "ሊነግረን የሚፈልገው ምንድን ነው?" የሚለው ጥያቄ ደጋግሞ ይመጣብኛል። ይህ የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ ምንነትን ለመረዳት የሚጥር ፖለቲካዊ መጣጥፍ ነው። ‘አዲሱ አራዳ’ ማነው? በዚህ ዘፈኑ በብዙዎቻችን ዕድሜ የትዝታ ማኅደር ውስጥ የሚገኙ ነገር ግን በአዲስ አበባ ልማት ሥም የፈረሱ እና እየተረሱ ያሉ ሰፈሮችን ሥም ያነሳሳል። ዘፈኑ በግጥሙም በዜማውም፣ የሐዘን እንጉርጉሮ ያለበት ነው። ምሳሌ እንውሰድ፦ “ጨርሰሽ ስትወጪ ከቡፌ ዳ’ላጋ፣ ጠብቂኝ እንዳልል፣ ቆመሽ መሐሙድ’ጋ፣ አገር ...