Skip to main content

“ይህ - የታገልንለትን ጉዳይ አለማወቅ ነው”

ኮሎኔል መንግስቱ ኃ/ማርያም በአንድ ወቅት በፈፀሙት ድርጊት ተፀፅተው ይቅርታ ይጠይቁ እንደሁ በገነት ‹ማስታወሻ› ላይ ሲጠየቁ ‹‹ማንን ነው ይቅርታ የምጠይቀው? ወያኔን? ወያኔ እኔን ይቅርታ ጠይቆኛል?...ይህ የታገልንለትን ጉዳይ አለማወቅ ነው›› በማለት ጥያቄውን በጥያቄ መልሰዋል፡፡ መንግስቱ በአስተዳደራቸው ማክተሚያ ሰሞንም፣ በመንግስት መገናኛ ብዙሐን እንዲህ ብለው ነበር፡፡ ‹‹ለአገሬና ለወገኔ ይበጃል ብዬ ባደረግኩትና በተሳተፍኩባቸው ተግባሮች ሁሉ በግሌ ሕሊናዬን የሚወቅሰኝ ነገር የለም›› ብለዋል፡፡

‹‹መ››ንግስቱ እና ‹‹መ››ለስ
መለስ በመንግስቱ ቆብ ውስጥ ገብተው ይሆን?

በመጀመሪያ የስልጣን ዘመናቸው ዲሞክራት  መስለውን ነበር::
እኛን ብቻ ሳይሆን ምዕራባውያንንም በዚህ ሸውደዋቸዋል::
ምዕራብውያን ታዛዥነታቸውን ስለሚወዱላቸው ብቻ ተቀብለዋቸዋል::
የመለስ ታዛዥነት ለውጭ ኃይሎች ብቻ እንጂ ለአገራቸው ሕዝብ
አይደለም::  መለስ በውጭ ዲፕሎማሲ ጎበዝ የሚመስሉዋችሁ ከሆነ -
አይደሉም:: ሊደራደሩበት የሄዱትን ጉዳይ አሳልፈው በመስጠት
መስማማትን ይመርጣሉ::  ውጪያዊ ተቃውሞ የማይደመጥባቸውም
ለዚያ ነው::

በዴሞክራሲ ጉዳይ "ሙጋቤ የሚለው አፍሪካውያን የምዕራባውያን
ዓይነት ዴሞክራሲ  አያስፈልጋቸውም::" ብሎ ነው ብለው መለስ
ከጋዜጠኛ ጋር ከተሟገቱ በኋላ የዴሞክራሲ  በኢትዮጵያ ተስፋው
ተመናምኗል:: ሙጋቤ  መንግስቱን አስጠልለዋል - አሁን ደግሞ
መለስም  የርሳቸውን የዴሞክራሲ ቲዎሪ እየዘመሩ ነው::
መንግስቱና መለስ እያደር የሚያመሳስላቸው ነገር ተበራክቷል፡፡ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ነጋሶ ጊዳዳ ‹‹የነጋሶ መንገድ›› በተሰኘው ግለታሪካቸው እንደነገሩን የሕወሓት ተገንጣይ ቡድን ተሸንፎ ሲወጣ የነመለስ ቡድን (በተለይ አቶ መለስ) ‹‹ጃኬታቸውን አስወልቀን ሸኘናቸው›› እያሉ ሲፎክሩ ነጋሶ መለስን ‹‹መንግስቱን፣ መንግስቱን መሰልከኝ›› ብለዋቸዋል፡፡ እውነት ነው፤ (መ)ንግስቱና (መ)ለስ (መ)ንትያ ናቸው፡፡ እስኪ በዝርዝር እንመልከተው…
  • አነጋገር - መለስ ንግግር አዋቂ ናቸው፡፡ መንግስቱም ንግግር አዋቂ ነበሩ፡፡ መንግስቱ ለቃላት አመራረጥ አይጨነቁም ነበር፡፡ ስድብና ድንፋታ በየአደባባዩ አያሳፍራቸውም ነበር፡፡ መንግስቱ ከወረዱ ከ20 ዓመት በኋላ እርሳቸውን ከስልጣን ያስወገዱት አማፂያን መሪም ይኸው የሳቸውን ፈር እየተከተሉ ነው፡፡ መለስ በየፓርላማው አባሎቻቸውን በሚያስቀው ስድባቸው አንጀታቸው ስለማይርስ - አሁን፣ አሁን የእጅ እንቅስቃሴያቸው እና የትከሻቸው መናጥ የስድብ አምሮታቸውን ያሳብቅባቸዋል፡፡
  • ነፍስ ማጥፋት - የመንግስቱ ኃ/ማሪያም ኢሠፓ ከተቃዋሚዎቹ ኢሕአፓ ጋር በከተማ መሃል ሽምቅ ውጊያ የጀመረው ገና በስልጣኑ አፍላ ዘመን ነው፡፡ ቀይሽብር እና ነጭሽብርን በየበኩላቸው አውጀው ሲገዳደሉ ስለወደፊቷ ኢትዮጵያ ዕጣ ፈንታ አላሰቡም ነበር፡፡ (ለመንግስቱ አምባገነንነት የኢሕአፓ ድርሻ ቀላል አይደለም) የአቶ መለስ ደግሞ ይብሳል፡፡ ደርግ አውጆ ሲገድል፣ ኢሕአዴግ ከቻለ በድብቅ/በሰበብ ካልቻለ ደግሞ ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም በአንድ ጽሁፋቸው ላይ እንዳሉት ‹‹don’t kill them, break them›› የተሰኘ ዘዴ ይከተላል፡፡ የመለስ ዜናዊ ሰራዊት የጥይት አሩሩን ያሳረፈው እንደኢሕአፓ የመሳሪያ ትግል በጀመሩ ተቃዋሚዎች ላይ አይደለም፡፡ ከድንጋይ መወርወር በላይ አቅም በሌላቸው ወጣቶች ላይ ነው፡፡
  • ስልጣን - መንግስቱ ለ17 ዓመታት ያህል መተኪያ ያልተገኘላቸው መራሄ መንግስት ሆነው ነበር፤ አሁን ደግሞ መለስ 25ኛቸውን ዓልመው እየተጓዙ ነው፡፡
  • ነፃነት - በደርግ ጊዜ መንግስትን መቃወም ቀርቶ ለመቃወም ማሰብም የሚያስፈራ ነገር ነበር፡፡ አሁንም ነገሩ ብዙ የተለየ አይደለም፡፡ ሁሉም ሰው መቃወም ይፈራል፤ በቀጥታም ባይሆን በተዘዋዋሪ ዋጋውን እንደሚቀምስ ያውቀዋል፡፡ የእንግሊዙ Legatum Institute አምና ባወጣው የProsperity Index ላይ ኢትዮጵያ በግለሰብ ነፃነት ከ110 አገሮች 93ኛ እና በሕዝቦቿ የደህንነት ስሜት ደግሞ 103ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠች የፈሪዎች አገር ሁናለች - የነፃነቱ ብዛት፡፡
  • ኢኮኖሚ - በደርግ ዘመን (ዕድሜ ለአማፅያን) መንግስቱ አብዛኛውን የበጀት ፈሰሳቸውን ለጦርነት በማዋላቸው የኢትዮጵያ ሕዝብ በረሃብና ችግር አለንጋ እየተገረፈ ነበር፡፡ አሁንም በመለስ ሕንፃዎች በሚፈሉበት፣ መንገዶች እየዘመኑ ባሉበት ዘመን ድህነት ከነኩራቱ ለ‹‹99 በመቶዎቹ›› ሕዝቦች ይታያቸዋል፡፡ ከላይ የጠቀስኩት ኢንዴክስም ይህንኑ ያረጋግጣል፤ ከ110ሩ ሃገራት 106ኛ ላይ የመለስ ኢትዮጵያ ትገኛለች፡፡

ስለዚህ መለስ ከመንግስቱ ይለያሉ ወይስ አይለዩም?

ማወዳደርን ምን አመጣው?
መለስ ራሳቸው አሁን፣ አሁን አስተዳደራቸውን ከመንግስቱ ዘመን አስተዳደር አንፃር መመዘን ጀምረዋል፡፡ ምነው እንኳን ባለፈው ኦስሎ ውስጥ ለገጠማቸው ተቃውሞ የሰጡት ማስተባበያ ‹‹በመንግስቱ ዘመን ሰዎች ሲገደሉ ለተገደሉበት ጥይት ሒሳብ ይከፍሉ ነበር›› አላሉም? ነገሩን የታዘቡት የአዲስ ነገር ጋዜጠኞች ‹የአገር ቤት ጋዜጦች› በተሰኘው ሳምንታዊ ክለሳቸው ‹‹መለስ ይህን ያሉት፣ አሁን እኛ ነን የጥይቱን ዋጋ የምንሸፍነው ለማለት ፈልገው ይሆን?›› ሲሉ ተሳልቀዋል፡፡

መለስ ማነፃፀር ከጀመሩ አይቀር እኔም አንድ ነገር ልጨምርላቸው፡፡ መንግስቱ ኃይለማርያም ሲታገሉ የነበረው ለምን እንደሆነ ማስታወስ ነበረባቸው፡፡ መንግስቱ ኃ/ማርያም ሲታገሉ የነበሩት፤ ለኢትዮጵያ አንድነት፣ ለኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ነበር፡፡ ከመለስ ሰራዊት ጋር ሲታገሉ በመክረማቸው ነበር አምባገነን አድርጎ ያስቀራቸው፡፡ (በርግጥ የርሳቸው፣ የፍላጎት ድርሻ ውስጡ ቢኖርም) የመንግስቱ አስተዳደር ከጊዜያዊ ወታደራዊ መንግስትነቱ ለመላቀቅ እንኳን ፋታ ሳያገኝ ነው በትግል ወጥቶ በትግል የኮበለለው፡፡ መንግስቱ የፈሩት አልቀረም፤ የኢትዮጵያ አንድነት በብሔር ዘመም አስተሳሰቦች ከተናጋ ውሎ አድሯል፣ የባሕር በር ባለቤትነታችንም ድሮ ቀረ፡፡

ምናልባት የመንግስቱን የጭካኔ ዘመን ስላልደረስኩበት ሊሆን ይችላል፤ ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን ለኔ ‹‹ለሰላም ሲባል›› የአገራቸውን ድንበር በሱዳንም፣ በሶማሌያም፣ በኬንያም፣ በኤርትራም በኩል እየቆረሱ ያልሰጡት፣ (መንገዱን ባያውቁበትም) ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያዊነት ያላቸው ፍቅር የማያጠያይቀው፣ ሚሊዬነር ሊሆኑ ቀርቶ ለራሳቸው ምንም ቅሪት ሳያጠራቅሙ የኖሩት መንግስቱ፣ ይህንን ሁሉ መሆን ካልቻሉትና ከእርሳቸው (ኮ/ል መንግስቱ) ስህተት መማር ካልቻሉት ከአቶ መለስ ይሻሉኛል፡፡

አሁን ደግሞ፤ ኮሎኔል መንግስቱ ‹ትግላችን› በሚል በፀሃይ አሳታሚ (ከአሜሪካ) አማካኝነት እያሳተሙት ባለው የመጀመሪያው ቅጽ መጽሃፋቸው ላይ ‹‹የፖለቲካ ድርጅቶችም ሆኑ መሪ ግለሰቦች የሚመጡና የሚሄዱ አላፊዎች ሲሆኑ ሃገርና ሕዝብ ግን ዘላለማዊ ናቸው፡፡ ይህም ቢሆን በአንድ ታሪካዊ ወቅት መንግስታት፣ የፖለቲካ ድርጅቶች ወይም ግለሰቦች ያከናወኗቸው ገንቢም ሆነ አፍራሽ ተግባሮች ማንም ወደደ ጠላ የዚያ ሃገርና ሕዝብ ታሪክ ናቸው›› ብለዋል፡፡

ታዲያ ለምን ይሆን መለስ ዜናዊ ከመንግስቱ የተሸሉ መሆን ባይችሉ እንኳን የመንግስቱ ኃ/ማርያምን ታሪክ መድገም ያስፈለጋቸው?

Comments

Popular posts from this blog

The "Corridor Development" is a Façade of the Prosperity Party

Befekadu Hailu I have seen a news report claiming that 40% of central Addis Ababa will be demolished for the corridor development; I am not able to confirm the validity of the news but it sounds real to me given the size of massive operations in the demolition of old neighborhoods and construction of bike lanes, green areas, and glittering street lights. I like to see some beauty added to my city but cannot help mourning the slow death of it too. Addis Ababa was already in a huge crisis of housing and the demolition of houses is exacerbating it. Apparently, Prime Minister Abiy Ahmed is eager to showcase his vision of prosperity by demonstrating how fast his administration can do magic by beautifying the front sides of the streets with lights, new pavements, and painted fences ("to fake it until he makes it" in my friend's words). Therefore, he and his party do not care about the miserable human stories behind the scenes and they will harass you if you tell it (Azeb Woku...

የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ

በፍቃዱ ዘ . ኃይሉ “የአዲስ አበባ ብሔርተኝነት” ቢኖር ኖሮ መሪው ልጅ ሚካኤል ይሆን ነበር። አሁን አሁን እሱ ስለ አዲስ አበባ የዘፈናቸውን ዘፈኖች ቁጥር ራሱ በትክክል መቁጠር ይቸግረኛል። ለአዲስ አበባ ከተዘፈኑ ዘፈኖቹ ውጪም በየዘፈኑ ውስጥ የሚጨማምራቸው መልዕክቶች በራሳቸው መወድሰ አዲስ አበባ ናቸው። ለምሳሌ፣ በቅርቡ በለቀቀው ‘አዲስ አራዳ’ በተሰኘው አልበሙ ውስጥ ‘የድሬ ልጅ’ የሚል ዘፈን አለው። ዘፈኑ የተዘጋጀው ያው የአዲስ አበባ እህት ተደርጋ የምትቆጠረውን ድሬ ዳዋን ለማወደስ ነበር። ልጅ ሚካኤል ግን የአዲስ አበባ ፍቅሩ ያመልጠውና የሚከተለውን ያቀነቅናል፦ “መጣልሽ በሏት፣ ድሬ ድረስ፣  ከአዱ ገነት፣ ከሸገር፣ ከአዲስ ደረሰ፣... የሸገር ልጅ አራዳ ነው፣ ሰው አክባሪ፣ ሰው ወዳዱ፣ ቀላጅና ተረበኛ፣ ፍቅር ይዞ የሚተኛ፣ ‘አለው’ የለ፣ ‘የለው’ የለ፣ ከሁሉ ጋ፣ ግባ ጀባ...፤” ፤ ልጅ ሚካኤል በዚህ አልበሙ ብቻ አዲስ አበባን የሚያውድሰባቸው ሌሎችም ዘፈኖች አሉ፤ ‘ አዲስ አራዳ ’ የሚለው የአልበሙ መጠሪያ እና ‘ሸገር’ የሚሉት ዘፈኖቹ ዋነኞቹ ናቸው። ታዲያ እንዲህ በአዲስ አበባ ፍቅር የሚቃጠለው ልጅ ሚካኤል "ሊነግረን የሚፈልገው ምንድን ነው?" የሚለው ጥያቄ ደጋግሞ ይመጣብኛል። ይህ የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ ምንነትን ለመረዳት የሚጥር ፖለቲካዊ መጣጥፍ ነው። ‘አዲሱ አራዳ’ ማነው? በዚህ ዘፈኑ በብዙዎቻችን ዕድሜ የትዝታ ማኅደር ውስጥ የሚገኙ ነገር ግን በአዲስ አበባ ልማት ሥም የፈረሱ እና እየተረሱ ያሉ ሰፈሮችን ሥም ያነሳሳል። ዘፈኑ በግጥሙም በዜማውም፣ የሐዘን እንጉርጉሮ ያለበት ነው። ምሳሌ እንውሰድ፦ “ጨርሰሽ ስትወጪ ከቡፌ ዳ’ላጋ፣ ጠብቂኝ እንዳልል፣ ቆመሽ መሐሙድ’ጋ፣ አገር ...

መጽሐፍ የሚወጣው፣ የተዋነይ ዘ ጎንጅ 5 መሥመር ቅኔ

ጎንጅ ቅኔ ያጠናበት ደብር ሥም ነው። ደብረ ጥበብ ጎንጅ ቅዱስ ቴዎድሮስ ገዳም። ተዋነይ የባለቅኔው ሥም ነው። (የግዕዝ ትርጉሙ "ዋናተኛ" ማለት ነው።) ሊቁ ተዋነይ የልኅቀቱን ያክል እምብዛም አይወራለትም፤ ነገር ግን በዘመኑ ወደር የሌለው ልኂቅ ስለመሆኑ ሥራው ይናገራል። የሕይወት ተፈራ "Mine to Win" የተሰኘ ድርሰት መቼቱን በዐፄ ዮሓንስ ንግሥና ዘመን፣ በጎጃም/ጎንደር የቅኔ መማሪያ ደብሮች ያደረገ ልብወለድ ነው። ልቦለዱ የቅኔ ትምህርት ስርዓትን ያስተዋውቀናል፤ በበኩሌ የቅኔ ትምህርትን እና የቅኔ ሊቃውንት ታላቅነት ቀድሞ ከነበረኝ ግንዛቤ የበለጠ እንዲሆን አድርጎኛል። በተለይ የተዋነይ ዘ ጎንጅ (በውኑ ዓለም የነበረ ባለቅኔ) ተከታይዋ አምስት መሥመር ቅኔ መጽሐፍ የሚወጣት እንደሆነች ልቦለዱ አሳሰበኝ። ወይም በአጭሩ ብዙ ምዕራባውያን ስንት መጽሐፍ የጻፉለት ፍልስፍናን በአምስት መሥመር ይዟል። የቅኔው ትርጓሜ የመጽሐፍ ቅዱስን እና የመጽሐፍ ቅዱሱን ፈጣሪ ኅልውና ይሞግታል። “የአምን ወይገኒ ኵሉ ዓለም በዘፈጠረ ለሊሁ ብዙኃን እንዘ ይገንዩ ይስግዱ ቅድሜሁ ለነጽሮ ዝኒ ነገር እሥራኤል ከመይፍርሑ ሙሴ ፈጠረ ፈጣሪሁ ወ ፈጣሪ ፈጠረ ኪያሁ።” (ተዋነይ ዘ ጎንጅ። ምንጭ፣ሕይወት ታደሰ ወደአማርኛ የተረጎመችው የሕይወት ተፈራ መጽሐፍ) ትርጉሙን በኋላ እመለስበታለሁ። ስለተዋነይ መጀመሪያ የሰማሁት የበውቀቱ መጽሐፍ ላይ ነበር። እሱም በጨረፍታ - “የሌሊት ዜማዎች” የሚለው ግጥሙ ውስጥ። በውቀቱ ተዋነይን በግጥሙ ግርጌ ማስታወሻው አስተዋውቆን ያልፋል፣ “ተዋነይ በቅኔ ቤት አፈ ታሪክ ሞትን በግዝት ለሰባት ዓመታት ያቆመ ጀግና ነው"። ከዚያ በኋላ፣ አዲስ አድማስ ላይ የወጣ አንድ ጽሑፍ ተዋነይ የተላከበትን ...