Pages

Friday, February 28, 2014

እኔ የምፈልገው ኢሕአዴግ ወርዶ ማየት ብቻ ነው!

ትላንት የጥላቻ ንግግርን የተመለከተ ጥናት ማሟያ ውይይት ላይ ተሳትፌ ነበር። በርዕሰ ጉዳዩ ላይ በሰፊው የምመለስበት ቢሆንም፥ ቀብዱን ግን እነሆ፦

ርዕሱ በኢሕአዴግ እና በደጋፊዎቹ አተረጓጎም "የጥላቻ ንግግር" ተብሎ ሊመደብ ይችላል። አንድ የዴሞክራሲ ሕልመኛ ርዕሱ ላይ የተጠቀሰውን ዓ/ነገር ቢናገር ኢ-ዴሞክራሲያዊም ሆነ ጥላቻ ሰባኪ አያሰኘውም ባይ ነኝ እኔ ግን። እኔ ራሴ ርዕሱ ላይ የተጻፈውን ያለምንም ጥላቻ ከውስጥ ፍላጎቴ ነው ያፈለቅኩት።

ከዴሞክራሲ ዐብይ ባሕርያት አንዱ ገዢ ፓርቲዎች ወርደው የሕዝብ ምርጫ በሆኑ ተቃዋሚዎች መተካት የሚችሉበት እና ገዢ የነበሩ ተቃዋሚ ሆነው የሚሮጡበት ስርዓት ማመቻቸት ነው። ስለዚህ ለኔ ኢትዮጵያ ለዴሞክራሲያዊነት መፍጨርጨሯ ሐቀኛ ነው ልል የምችለው ኢሕአዴግ ወርዶ ተቃዋሚ ሆኖ ሳየው ነው።

የጥላቻ እና የፍቅር ንግግሮች የሉም ማለት አልችልም። ነገር ግን የጥላቻም ይሁን የፍቅር ንግግሮች ዋጋቸው ከአንድ ክበብ አያልፍም። ለምሳሌ ኢትዮጵያ ነክ የአገር ውስጥ እና የውጭ ሚዲያዎች በባሕሪያቸው መድባቸው ብባል በሦስት እመድባቸዋለሁ፦
1ኛ) አፍቃሬ-ኢሕአዴግ፣
2ኛ) ኢሕአዴግን-አያሳየኝ እና
3ኛ) I-don't-know-what-to-doዎች በማለት።

የመጀመሪያዎቹ [አፍቃሬ-ኢሕአዴግ]ዎቹ ዋነኛ ሥራቸው በማንኛውም መንገድ ኢሕአዴግን ማንቆለጳጰስ እና ከተቃዋሚዎች ክፉ ዓይን መጠበቅ ናቸው። አዳም ሲፈጠር ጀምሮ "በስም መስጠት ነው (naming)" ነው ሥራውን የጀመረው እንዲሉ እኔም በዚህ ምድብ የምፈርጃቸውን ጥቂቶች ልዘርዝር፤ ኢቴቪ፣ ዛሚ ኤፍኤም፣ ኢትዮ-ቻናል፣ ትግራይ ኦንላይን እና ወዘተ ናቸው።

ሁለተኛው ምድብ ውስጥ የሚገኙት [ኢሕአዴግን-አያሳየኝ]ዎች ደግሞ የሚደግፉት (የሚያፈቅሩት) የተለየ የተቃዋሚ ቡድን የላቸውም፣ የሚራሩለት እንጂ። ነገር ግን ያለምንም ጥርጥር ኢሕአዴግን አይወዱም። ስለዚህ ሥራቸው ኢሕአዴግን መተቸት ነው። እነዚህ ውስጥ ኢሳት፣ ፋክት፣ ኢትዮጵያን ሪቪው እና ወዘተ ይገኛሉ።

ሦስተኛው ምድብ [I-don't-know-what-to-do]ዎች ውስጥ ያሉት ደግሞ በመሐል ቤት ይዋልላሉ። ለዚህ ቡድን አሪፍ ምሳሌ የሚሆኑት ደግሞ አዲስ አድማስ ጋዜጣ እና ሸገር ኤፍ ኤም ናቸው። በተረፈ ጥቂቶች ብቻ ለመፈረጅ የማይመች የሚዲያ ሥራ እና ሊረዱት የሚከብድ የአቋምና አቀራረብ ልዩነት ያሳያሉ።

ለምን እነዚህን ፍረጃዎች እና ስየማዎች ማድረግ አስፈለገኝ? ምክንያቱም የጥላቻ ንግግሮች በማን፣ እንዴት እንደሚተረጎም ቀላል ማስረጃ ስለሚሆነኝ ነው። ምድብ አንድ ውስጥ ለሚገኙ ማንኛውንም ዓይነት ኢሕአዴግ ላይ የተሰነዘረ ትችት የጥላቻ ንግግር ነው።
ምድብ ሁለት ውስጥ ለሚገኙትም ከኢሕአዴግ አፍ የሚወጣ ሁሉ ክፉ ነገር ነው። ሦስተኛው ምድብ ከቻለ ሁሉንም ለማስደሰት ካልቻለ ሁሉንም ላለማስከፋት ይፈጨረጨራል። በመሐል ቤት እውነት ማደሪያ ታጣለች። ሁሉም ለዓላማው እጇን ይጠመዝዛታል።

በአገራችን የጥላቻ ንግግር የሚባሉት ሁሌም ከጥላቻ የመነጩ ላይሆኑ ይችላሉ። በባሕላችን የሰውን ስህተት ፊት ለፊቱ መንገርን እንደአለመከባበር የሚያስቆጥር ስህተት ነው። ስለዚህ የአንድን ሰው ጉልህ እንከን እንዲህ ነህ ብሎ መንገር በጣም አስደንጋጭ ነው የሚሆነው። እንዲያውም በጠብ ወቅት ብቻ የሚከሰት ነገር ነው። ስለዚህ በትልቁ (በፓርቲና በፖለቲካዊ አመለካከት ላይ) ሲሰነዘር የእርምት አስተያየት መሆን ቀርቶ የትችት ማዕረግ እንኳን አያገኝም። የጥላቻ ይመስላል (ይባላል)።

ነገር ግን፤ ድክመትን እየሸሸጉ ብርታትን እንደመንገር ያለ አደገኛ ንግግር (dangerous speech) አይቼም ሰምቼም አላውቅም። ለግለሰብም ይሁን ለቡድን ግብዝነት ይዳርጋል። ድክመት ሲነገረው እልል ብሎ በፈገግታ ተጉመጥምጦ የሚውጥ ግለሰብም ይሁን ቡድን ገጥሞኝ አያውቅም፤ ከትችቱ አለመማር ግን እየሰሙ አይቻልም፤ ከስህተት ላለመማር መፍትሔው እንደኢሕአዴግ ተቺውን ማፈን ብቻ ነው። ትችት ካደመጡት ግን ምናልባት ለመዋጥ ጊዜ ይወስድ ይሆናል እንጂ ዘልቆ መቆጥቆጡ አይቀሬ ነው።

ይሄ ሁሉ ግን ስለጠሉ ብቻ የሚተቹ፣ ስለወደዱ ብቻ የማይሞገሰውን የሚያወድሱ የሉም ማለት አይደለም። ጥላቻና ፍቅርም ምክንያታዊ አይሆኑም ማለት ይከብዳል። ነገር ግን ክርር ያሉት የሥነ ልቦና ዕርዳታ ያስፈልጋቸዋል።

የጥላቻ ንግግርን መብት ከሐሳብን የመግለጽ መብት ለይቶ ለማስቀረት ሁነኛው መፍትሔ የማንፈልገውን ብቻ ሳይሆን የምንፈልገውንም ጭምር ማወቅ አለብን፤ አራማጅ ተራማጅነታችንም በመርሕ እንዲመራ ማድረግ መድኃኒቱ ነው።

Tuesday, February 25, 2014

አድዋን መዘከር፤ በአርበኞቹ መንገድ!


በመጀመሪያ እንዲህ ነበር - የሬይሞንድ ጆናስ ‘The Battle of Adwa” (የሙሉቀን ታሪኩ ትርጉም)፣ ቅድመ አድዋ ላይ የነበረውን የአውሮጳውያን ስሜት ሲገልጽ የአሜሪካኑ አትላንታ ኮንስቲቲውሽን ጋዜጣ የጻፈውን አጣቅሶ ነበር፤
‹‹መላዋ አፍሪካ በአውሮጳ መንግሥታት ቅርምት የምትጠናቀቅበት ቀን ቀርቧል፤ አውሮጳውያኑ በአሜሪካ ያሳኩትን የዘር የበላይነት በአፍሪካ ለመድገም ተዘጋጅተዋል፡፡ በአሜሪካ ቀይ ሕንዶችን በማስወገድ ለራሳቸው ዝርያ መኖሪያ መፍጠር የቻሉበትን ብቃት በአፍሪካ ለመድገም የጥቁር አፍሪካ ዝርያዎችን በቅርቡ ማጥፋት ይጀምራሉ፡፡››
ይህ የአውሮጳውያን ሕልም ቅዠት ሁኖ የቀረው በአድዋ ድል ድባቅ ሲመቱ ጀምሮ ነው፡፡ ይህ የድል በዓል ከየትኞችም የድል በዓላት በላይ ደምቆ ቢከበር አያንስበትም፡፡ ለነገሩ፣ ይህንን በቅጡ የተረዱ እና እውን ለማድረግ የሚፍጨረጨሩ ኢትዮጵያውያን አሉ፡፡

የካቲት 23፣ 1988 በአድዋ ተራሮች በተካሄደው ጦርነት የተደመደመው እና ጥቁሮች በታሪካቸው ለመጀመሪያ ግዜ ነጭ ወራሪን በጦር ሜዳ አሸንፈው የታዩበት ‹‹የአድዋ [ዕ]ድል›› በዓል ዘንድሮ በልዩ ሁኔታ 118ኛውን ልደቱን ያከብራል፡፡ የዘንድሮው አከባበር ለከርሞው እና ለ120ኛው ደማቅ አፍሪካ አቀፍ አከባበር መሠረት ይጥላል ተብሎ ይታሰባል፡፡ በዓሉን ለማድመቅ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እያደረጉ ካሉት ሰዎች በአንዱ የተለመደ አባባል የዚህን ጽሑፍ ዓላማ በመጠየቅ ልጀምር፤ ‹‹በዓሉን ከወትሮው የሚለየው ምንድን ነው? የበዓሉ አከባበር አስተባባሪዎች እነማን ናቸው? በዓሉን በሚያስተባብሩበት ወቅት ምን ፈተና ገጠማቸው?›› ለሚሉትና ሌሎችም ጥያቄዎች መልስ፥ ከአስተባባሪዎቹ አንዱ የሆነውን ያሬድ ሹመቴን ከሚገኝበት አድዋ አካባቢ በስልክ አነጋግሬዋለሁ፡፡ ዝርዝሩን እነሆ፡-

ጉዞ አድዋ

የአድዋ ከተማ ከአዲስ አበባ 1000 ኪሎ ሜትር ይርቃል፡፡ ከጥቂት ፈረሰኞች በቀር አብዛኛዎቹ አርበኞች ጣልያንን ለመግጠም ወደስፍራው የተጓዙት በእግራቸው ነበር፡፡ ያንን የተጋድሎና የነጻነት ጉዞ ከጦርነት ወዲህ ያለውን ለመድገም የተዘጋጁ አምስት ሰዎች ድንኳናቸውን አዝለው በእግር ተጉዘው አድዋ በድሉ መታሰቢያ ዕለት ሊገቡ በማቀድ ጥር 10፣ 2006 ጀምረው እየገሰገሱ ነው፡፡ እነዚህ እግረኞች በኢትዮፒካሊንክ አዘጋጅነቱ የምናውቀው ብርሃኔ ንጉሤን ጨምሮ፣ መሐመድ ካሣ፣ ኤርምያስ ዓለሙ፣ ሙሉጌታ መገርሣ እና ዓለምዘውድ ካሣሁን ናቸው፡፡ በደጀንነት (በማስተባበር) ያሬድ ሹመቴን ጨምሮ ሌሎች ሦስት ሰዎች በመኪና እያጀቧቸው፣ ሒደቱን እየተከታተሉ እና በካሜራ እያስቀሩ ነው፡፡

ያሬድ ሹመቴ የ‹‹ጉዞ አድዋ›› ዓላማ ሁለት ነው ይላል፤ የመጀመሪያው የአድዋ ድልን እና የተከፈለለትን መስዋዕትነት መዘከር ሲሆን፥ ሁለተኛው ይህንን ድንቅ ታሪካዊ ድል እስከ ‹‹ጥምቀት በዓል አከባበር›› የሚደርስ ያለ ደማቅ አከባበር እንዲያገኝ ፈር ለመቅደድ ሲባል የተዘጋጀ ነው፡፡

የ‹‹ጉዞ አድዋ›› አርበኞች መንገዳቸውን ከጀመሩ ዛሬ 41ኛ ቀናቸው ነው፡፡ ጠቅላላ ጉዞው ይፈጃል ተብሎ የተገመተው 43 ቀናት ሲሆን እስካሁን የተጓዙት በታቀደው መሠረት ነው፡፡ በየዕለቱ ከ25 እስከ 30 ኪሜ ድረስ እየተጓዙ ነው፡፡ አጭር የተጓዙበት ዕለት 12 ኪሜ ብቻ የተጓዙበት ዕለት ነው፡፡ ረዥም ጉዟቸው ደግሞ አጭር የተጓዙበትን አራት እጥፍ ይጠጋል፤ 47 ኪሎ ሜትር በአንድ ቀን! ይህንን ጉዞ ያደረጉት ከካራቆሬ እስከ ከሚሴ ድረስ ነበር፡፡

Uganda Law Provoked Ethiopian Discussion



Uganda’s president, Yoweri Museveni, passed an anti-gay bill into law on February 24, 2012. As the news broke, twitter went into hot discussion among people who support and reject the President’s decision. Ethiopians also took part in the discussion. Ethiopia, a country itself criminalized ‘homosexuality acts’ in its penal code for many decades, has a large community who blindly rejects the discussions on topics of sexuality let alone legalizing it.

Many of the tweets were reflected after Ethiopian Minister of Women, Children and Youth Affairs, Zenebu Tadesse, who broke the silence tweeting:

There is no place for hate, discrimination in my beloved Africa. It's not Governments' business to make dress code or anti-gay laws. #Uganda.
Many applauded her tweet; however, a few questioned whether the tweet is her opinion or her government’s position. Eyob A. Balcha asked:

Your Excellency, what's your government’s position on same sex-relation? As far as I know, it's illegal in Ethiopia.
Rediet suggested the minister to use ‘views are my own’ tag, if her tweets don’t reflect her government’s stance:
Should we take this tweet as your opinion or the government office you are representing? If not, best to use 'views are my own' tag.
Aklilu H. Wold said it is not morally right to advocate this while being a minister of women and children:
Being a minister of women and children, [it’s] not morally right to advocate against anti-gay law. How about in Ethiopia?
The minister replied today:

ብዙአየሁ “የማ[ላ]ቃትን" ሴት አስናፈቀኝ

"የሚጣፍጥ ሕመም ስሜት ነው፣ ቅር የሚል ደስታ፣
ሙሉው ጎዶሎ ነው ትርጉሙ ትዝታ፤"
ወትሮም፣ እመንገዴ ላይ "ትዝታ" ሙዚቃ የተከፈተ እንደሆን ሁሉም ነገር ቅዝቅዝ፣ ፍዝዝ፣ ድንግዝ ይልብኛል። አረማመዴ፣ የጄ ውዝዋዜ፣ ሁለ ነገሬ ስክን ብሎ ልክ እንደ ዝግታ የተንቀሳቃሽ ምስል እንቅስቀሴ (slow motion) ይሆንብኛል።
"ከኔ አንጀት ይመስል፥ የተሰራው ክሩ
ይረበሻል ሆዴ፥ ሲገረፍ ክራሩ፤"
የላይኞቹን የግጥሙን [የሕዝብ?] ስንኞች ከመስማቴ በፊት የብዙአየሁ 2ተኛው ትራክ የሰጠኝ ስሜት ይህንኑ ነው። መጀመሪያ ላይ ያደመጥኩት ጠዋት፣ ጠዋት ማኪያቶ የምጠጣበት ካፌ ውስጥ ነበር። የዚህ ጽሑፍ ከፊሉ የተጻፈውም እዚያው ነው። ዲጄውም የኔ ዕጣ ሳይገጥመው አይቀርም፤ ይደጋግመዋል። አስተናገጋጆቹም አብረው እያዜሙ ያስተናግዳሉ። በኋላ ላይ ግን በየታክሲው ሁሉ አደምጠው ጀመር።

አሁን በዚሁ ዜማ የተሰየመው 'ሳላይሽ' የተሰኘው ሙሉ አልበም አለኝ፤ ነገር ግን ከዚህንኛው ዘፈን በቀር ትዝ የሚለኝ ሌላ ዘፈን የለም። እርግጥ ዘፈን ሳደምጥ የሆነ ሥራ እየሠራሁ ወይም የሆነ ዐሳብ እያሰብኩ ስለሚሆን ሙሉ ልቤን አልሰጠውም። ልክ እንደዚህኛው ልቤን የሚገዘግዘኝ  ካልመጣ በቀር የሰማሁት ምን እንደሆነ የማወቅ ዕድሉም ላይኖረኝ ይችላል።

ሙዚቃ ለኔ ስሜት ቆስቋሽ ከሆነ አሪፍ ሙዚቃ ነው ማለት ነው። የሚቀሰቅሰው ስሜት የምንም ይሁን፣ የምን በዜማው ሰው ማስቆዘምም ሆነ የሙድ ማፍታታት ማድረግ ከቻለ አለቀ! በእነሰርፀ ፍሬ ስብሐት ግምገማ ግን ከዚህ የተለየ ሊሆን ይችላል።…

ወደተነሳንበት ወግ ስንመለስ ብዙአየሁ እንዲህ ይላል፦
"ተስለሻል እንዴ ባይኔ በመሐሉ፣
አንቺ ብቻ እኮ ነሽ በሚታየኝ ሁሉ፤"
ዓይኔን ጨፍኜ ትታየኛለች እንዴ ብዬ ሳስብ አትታየኝም። ከዚያ ዘፈኑን የወደድኩት በዜማው ውበት እንጂ በገዛ ትዝታዬ አይደለም ብዬ አልኩ፤ ጥያቄው ግን "ትታየኛለች/አትታየኝም" ብዬ ያልኳት በስመ ፆታ ሔዋን ነው ወይስ…? ከዚህ ጥያቄ በኋላ ነው የዚችን ጽሑፍ ርዕስ "የማላውቃትን" ካልኩት በኋላ 'ቃ'ን ለይቼ በሳጥን ቅንፍ ውስጥ ያሰርኳት፤ ብትወጣም ስህተት የለውም እንደማለት።

ግጥም ያለው ዜማ ስንሰማ የምንወደው ግጥሙን ነው ዜማውን የሚለው ጥያቄ ሁሌም እንደፈተነኝ ነው። ብዙ ጊዜ ራሴን፣ ከዘፈን ግጥሞች ጋር አቆራኝቼ አገኘዋለሁ። ለምሳሌ የአብዱ ኪያርን ዜማዎች የምወዳቸው በግጥሞቹ ነው። ግን ደግሞ መልሼ ግጥሞቹን ያለዜማ ስሰማቸው ጣዕም አልባ ይሆኑብኛል። ስለዚህ ዜማ የሚወደደው ከግጥሙ ተጣምሮ ነው ወደሚለው ድምዳሜ ያጠጋጋኛል።
ሙዚቃ በጥቅሉ ባይኖር ኖሮ ዓለማችን የተለየ ማኅበራዊ ገጽታ ይኖራት ነበር ብዬ አምናለሁ። ገጽታው ምን ዓይነት ሊሆን እንደሚችል አልገምትም፤ እኔ ግን የምወደው ዓይነት የሚሆን አይመስለኝም። 

ትዝታ ግን አሁንም ይለያል። ትዝታን የኢትዮጵያውያን typical መለያ አድርጌ እወስደው ነበር። ያለፈ ነገር እንወዳለን። ዛሬ የፈለገ ቢሻል እንኳ "የዛሬን አያርገውና…" ማለታችን አይቀርም፤ "ድሮ ቀረ" ከአፋችን አይጠፋም። ከዛሬ ይልቅ የድሮው ትዝታ ይመስጠናል፣ ልጆቻችንን ዘመናዊ ዥዋዥዌ እያጫወትን የራሳችን የአፈር ሸርተቴ ይናፍቀናል። ተረስቶ እንዲቀር አንፈልግም። የትዝታ ዜማ ነገር ግን አሁንም ይለያል። ሌሎቹ ዓለማት ባይኖራቸው እንጂ ቢኖራቸው ኖሮ እንደሚወዱት አያጠራጥርም። በተለይ ጎልማሳ ለሆነ ሰው፣ ትዝታ ፍቱን መድኃኒት ነው። እንደኛ ሕመሞቹን ያለ ምንም ሥነልቦናዊ ዕርዳታ ለሚያክም ሰው፣ የትዝታ ዜማ ከሙድ አራቂነትም በላይ ነው። ለዚህም ነው የትዝታ ንጉሡ ማሕሙድ 'መዝገበ ቃላቱ ትዝታ ባይኖር ኖሮ የፍቅር ዕድሜው ያጥር ነበር' ያለን በዜማው።

በቃ የብዙአየሁ ዜማ ማለት ከላይ የቀባጠርኩትን ሁሉ የሚያስቀባጥር ነው።

Monday, February 17, 2014

‹ጠላፊው› vs. ‹አጋቹ› - ኢትዮጵያ vs. ስዊዘርላንድ

ዘላለም ክብረት

ዛሬ በጠዋቱ ዜናው በሙሉ ከአዲስ አበባ ወደ ሮም ሲጓዝ የነበረን 202 ሰዎችን ያሳፈረ የኢትዮጵያ አውሮፕላን 'መጠለፍ' ጉዳይ ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ኮሙንኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር ‹ጠላፊው ካርቱም ላይ የተሳፈረ ሰው ይመስላል› ቢሉም በመጨረሻ አውሮፕላኑ ካርቱም ላይ ከነጭራሹ እንዳላረፈና ጠላፊውም ረዳት ፓይለቱ እንደሆነ ተረጋግጧል፡፡ ረዳት ፓይለቱ ለምን ይሄን ተግባር እንደፈፀመ ሲጠየቅም ኢትዮጵያ ውስጥ መኖር ስጋት ላይ እንደጣለው በመግለፅ፤ ሲዊዘርላንድ ጥገኝነት እንድትሰጠው ጠይቋል፡፡

 ይህ ከሆነ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ የስዊዘርላንድ አቃቢ ሕግ መስሪያ ቤት እንደገለፀው ግን ጉዳዩ ጠለፋ (Hijacking) ሳይሁን እገታ ( Hostage Taking) ነው ብሏል፡፡ በሌላ በኩል ረዳት ፓይለቱ ወደ ኢትዮጵያ ተላልፎ እንዳይሰጥ ስዊዝን ተማፅኗል፡፡ ሁለት የህግ ጥያቄዎች አሉ፡

1. ጠለፋ ወይስ እገታ?

2. በረዳት ፓይለቱ ላይ የዳኝነት ስልጣን (Legal Jurisdiction) ያለው አካል ማነው? ኢትዮጵያ ወይስ ስዊዘርላንድ?

እነዚህን ጉዳዮች የሚፈቱልን ሁለት አለማቀፍ ሕጎች አሉ (ኢትዮጵያም ስዊዘርላንድም የሁለትም የሕጎቹ ፈራሚ ሀገራት ናቸው)፡፡

1. Convention for the Suppression of Unlawful Seizure of Aircraft – Hijacking Convention on Hijacking – 1970 &,

2. International Convention Against the Taking of Hostages – Convention on Hostage taking - 1983.

በነዚህ ሁለት ሕጎች መሰረትም የረዳት ፓይለቱን ሁኔታ (Situation ) እንይ፡፡

Saturday, February 15, 2014

Is Ethiopianism Re-examined or Replaced by Ethnopianism?

‘Ethiopiawinet' is an Amharic term equivalent to ‘Ethiopianism'. But, the context it is recently being discussed in social media is very different from it has been used in English and historical scripts. The old Ethiopianism (as written in the scripts) is more theological thought than political, and pan-Africanist concept than Ethiopian nationalist. The debate now ranges from denying the existence of it (as a self-standing identity) to worshiping it (as the only thought to save Ethiopian unity). The former is mainly opinion of ethno-nationalists who have concerns that the term might be used as pseudo-Abyssinian. They think the so-called ‘Ethiopianism' is not inclusive of all but is just an identity built on the cultures and religion of Ethiopian highlanders. I am guessing the debate ends with a new definition of what Ethiopianism is (should be). It seems Ethno-nationalism (which I would like to call Ethnopianism) is its biggest challenge.

Encyclopedia Britannica described Ethiopianism as “religious movement among sub-Saharan Africans that embodied the earliest stirrings toward religious and political freedom in the modern colonial period. The movement was initiated in the 1880s when South African mission workers began forming independent all-African churches, such as the Tembu tribal church (1884) and the Church of Africa (1889). An ex-Wesleyan minister, Mangena Mokone, was the first to use the term when he founded the Ethiopian Church (1892). Among the main causes of the movement were the frustrations felt by Africans who were denied advancement in the hierarchy of the mission churches and racial discontent encouraged by the colour bar. Other contributing factors were the desire for a more African and relevant Christianity, for the restoration of tribal life, and for political and cultural autonomy expressed in the slogan “Africa for the Africans” and also in the word Ethiopianism.

“The mystique of the term Ethiopianism derived from its occurrence in the Bible (where Ethiopia is also referred to as Kush, or Cush) and was enhanced when the ancient independent Christian kingdom of Ethiopia defeated the Italians at Adwa in 1896."

It was Garvey who first demanded ‘Africa for Africans'. A Study of Ethiopianism in Rastafarianism with a Focus on the Concept Of Ethiopia as Zion (by Jennifer Skowera) stated that ‘the man most responsible for bringing the ideals of Ethiopianism to Jamaica is Marcus Garvey. Barrett describes the man as ". . . the prophet of African redemption . . . [and through him] the spirit of Ethiopianism came into full blossom" (77).’

The term was  first coined in a desperate attempt of strengthening Africans and black people who were under colonization and slavery around the world. It is a huge ideal which conceived free and united Africa. That dream was big and isn't fulfilled yet.

Every sane African loves the idea of United Africa and even most pragmatic politicians want to come to it through regional integration of the east, of the west, of the north, of the south and of the center. As compared to this dream, it is difficult to grasp that how African countries are splitting into many for little differences. In east Africa alone, the number of countries is doubled within two decades.

These things happen because immature but accidentally influential politicians misunderstand systematic-inequality as inability to co-exist. In the process of states making and independence, some people were disproportionately favored. However this doesn't mean that [due to historical injustices,] the favored and disfavored ones can't exist together, many a self-claimed freedom fighters come and plant hate among people. In this way, the dream of African Union walks two steps away as Africans walk to have it a step.

The case in Ethiopia isn't different. Ethiopia is a small Africa where state fails to bond its people beyond tribal differences.

Discussions on Ethiopianism (as in unity and pride) give more sense to other Africans than us. That's why we need to stop and realize that unity is not the enemy of equality. Unity isn't becoming one but untied for better. Perhaps, it is because we aren't united that dictatorship isn't gone.

Thursday, February 13, 2014

የፖለቲከኞቻችን ሰው ፊት አቀራረብ (Presentability)

ፖለቲካ ጥበብ ነው፤ አንዳንዶች 'የማመቻመች ጥበብ'፣ አንዳንዶች 'የማጭበርበር ጥበብ'፣ ሌሎች 'art of possible' ይሉታል። አንዳንዴ እውነተኛ የሕዝብ ተቆርቋሪዎች እያሉ አስመሳዮች ያሸንፋሉ፤ ሐሳብ አፍላቂዎቹ እያሉ ሰራቂዎቹ ይመሰገናሉ። ሌሎች ፖለቲካ ጫወታ (game) ነው ይሉታል። ለብዙዎች የጨቀየ ጫወታ ነው፤ ለጥቂቶች ግን ጥበብም ጫወታም ነው። ተጫዋቾቹ ደግሞ በጨዋታው ሕግ (rule of the game) መሠረት መጫወት አለባቸው።

በእኛ አገር 'ፖለቲካ' እና 'ፖለቲከኝነት' ዛሬም አፍላ ነው። እስከዛሬ ጉልቤው ገዢ ነው፣ ገዢው ወሳኝ ነው። ምንም ዓይነት ፖለቲካዊ ጥበብ የሚጠይቅ የፖለቲካ ፉክቻ የለም። በአገራችን የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕድሜ 40 አይሞላም። በጠብ መንጃ ተነድቶ ሥልጣን ላይ የወጣ እንጂ በፖለቲካ ፉክክር ተንጓሎ የወጣ ፓርቲ የለም።

የፖለቲካ ፓርቲዎች ተቃዋሚ እና ገዢ ተብለው ፉክክር ውስጥ የገቡት በኢሕአዴግ ዘመን ነው። ሆኖም ከምርጫ 97 በኋላ ኢሕአዴግ በዴሞክራሲ ጉዳይ ላይ ስልታዊ ማፈግፈግ በማድረጉ ፓርቲዎች ትግሉን ከዜሮ እንዲጀምሩ አስገድዷቸዋል፤ ያውም በጠበበ ምኅዳር።
ከምርጫ 97 ወዲህ በተደረጉ የፖለቲካ ሽኩቻዎች ውስጥ ኢሕአዴግ በዝረራ ያሸነፈባቸው አጋጣሚዎች ብዙ ናቸው። ለዚህ መንስኤው ከኢሕአዴግ ዴሞክራሲያዊ ንፉግነት ባሻገር የተቃዋሚዎቹም ድክመት ተጠቃሽ ነው። ተቃዋሚዎች ፕሮግራሞቻቸውን በማስተዋወቅ እና ደጋፊ በማበርከት ረገድ ጉልህ ችግር አለባቸው። ሕዝቡ ተቃዋሚ መሆናቸውን አውቆ እንዲሁ እንዲመርጣቸው ይፈልጋሉ እንጂ የሚመርጥበትን ምክንያት ሊያስረዱት አይከጅሉም። ስለተቃዋሚዎች ድክመት ብዙ ተብሏል፤ እኔም አሁን አንዱን ነቅሼ ላወራ ነው - ሰው ፊት አቀራረብ (presentability)።

Monday, February 10, 2014

ልማታዊ አራማጅነት

ምስራቃውያን "ልማታዊ መንግሥታት ናቸው" የተባሉት በምዕራባውያን ነበር።  የኢትዮጵያ መንግሥት ግን ራሱ ነው "ልማታዊ" በማለት ራሱን መጥራት የጀመረው። ከዚያ በኋላ ቃሉ፣ በመንግሥት ኃላፊዎችና በተለይም በኢቴቪ በተደጋጋሚ ከመነሳቱና ካለቦታው ከመደንጎሩ የተነሳ የሚወክለው መንግሥት የሚከተለውን የኢኮኖሚ ስርዓት መሆኑ ቀርቶ በቀላሉ ሲታይ "የሚጠፉ ጥፋቶችን እንዳላየ አልፎ፥ ስለሚለሙ ልማቶች ብቻ ማውራትን"፣ ወይም በጥልቁ ሲመረመር "ገዢው ፓርቲን ከነቆሻሻው መደገፍን" ይመለከታል። ራስን ማዕረግ የመስጠት ጦሱ ይኸው ነው።

ኢሕአዴግ ደጋፊዎቹን ወጣቶች "የልማት ሠራዊት" ነው የሚላቸው፤ ቀሪው እንደጥፋት ሠራዊት ነው የሚቆጠረው። ሌላው ቢቀር ሁለቱንም አለመሆን አይፈቀድለትም። ኢሕአዴግ ራሱን ብቻ ልማታዊ አድርጎ የመቁጠሩ ነገር በስህተት የመጣ አይደለም፤ የፖለቲካ ፍልስፍና ጉዳይ ነው።

በተለይ ሰሞኑን ፓርቲው በመንግሥትነት ስሙ ተጠቅሞ በሚያዘጋጃቸው ስብሰባዎች ላይ የታይዋን እና ደቡብ ኮርያ ስም ተደጋግሞ በምሳሌነት ይጠቀሳል፤ ሁለቱም "ለልማት ሲባል ዴሞክራሲን ሰውተው ነው እዚህ የደረሱት" በሚል። ልማታዊነት ለዴሞክራሲ አያጣድፍም እንደማለት።
ክፋቱ ኢሕአዴግ እምነቱን በፀባይ ለማሳመን አለመፈለጉንም ይጨምራል። እንዲህ እያለ እያወራም ግን 'ዴሞክራሲያዊ ነኝ፣ ያለመሆን ፍላጎትም የለኝ' እያለ በአደባባይ እየዋሸ ያታልላል። ግን መልሶ፣ "ሁሉም ነገር ወደልማታዊነት ግንባር" ይላል - በራሱ የልማታዊነት ብያኔ። የለም፣ እኔ በራሴ ብያኔ እሠራለሁ ብሎ ነገር የለም። ለምሳሌ፤

Saturday, February 8, 2014

የሌለውን ልማት መካድ



ሰሞኑን በአዲስ ዘመን እና ኢዜአ ‹‹ጥናት›› ስም ገበያ ላይ ከወጡ አዲስ አባባሎች ውስጥ ‹‹ልማቱን መካድ›› የሚል ይገኝበታል፡፡ አባባሉ እንዲህ እንደዛሬው ጥናታዊ ዕውቅና አላገኘም ነበር እንጂ እንዲሁ በገደምዳሜው ግን ስሙ ይታወቅ ነበር፡፡ ኢሕአዴግ እና ቲፎዞዎቹ ‹‹ተቃዋሚዎች ልማቱን ይክዳሉ›› ይላሉ፤ ልማቱ የኢሕአዴግ ትልቁ መንጠልጠያ ነው፡፡

ራሱን ‹‹ልማታዊ መንግሥት›› ብሎ የሚጠራው የኢትዮጵያ መንግሥት ‹ሥልጣኑን ጠቅልዬ መያዝ የሚኖርብኝ እና ዴሞክራሲ ለመንፈግ የተገደድኩት ልማቱን ለማፋጠን ብዬ ነው› ይላል፡፡ አባባሉ ‹እኔ ሥልጣኑ ላይ ካልቆየሁ ልማት አይኖርም› የሚል ይመስላል፤ ሌሎች ልማት ማምጣት ስለማይችሉ ይሁን እነሱ ሥልጣን ላይ ከሌሉ አገሪቷ ላይ ሌላ ኃይል እንዳይመጣ ጦርነት ስለሚከፍቱ እኔንጃ - ልማቱ የሚጨናገፈው በምን እንደሆነ ተናግረው ግን አያውቁም፡፡ መቼም ልማት ማለት ግንባታ ሆኗል እና የግንባታ መሣሪያዎቹን እና መሥሪያ ቦታዎቹን ይዘው ከሥልጣን አይወርዱም ብለን እናስባለን፡፡

መታወቂያዬ ላይ “ኢትዮጵያዊ" ተብሎ እንዲጻፍ እፈልጋለሁ

ራስን "ኢትዮጵያዊ" ብሎ መጥራት ነውር እንዲመስል ጠንክረው የሚሠሩ አሉ። አልተሳካላቸውም ብዬ አልዋሽም። ምክንያታቸው እስከዛሬ የነበረው ኢትዮጵያዊነት አማራ ለበስ ነው፤ የዘውግ ብሔርተኝነት አንጂ ኢትዮጵያዊ ብሔርተኝነት (ማንነት) ብሎ ነገር የለም የሚለው ነው። መነሻ ነጥቡ እውነት ላይ ቆሞ፣ መድረሻው ግን ተራ ድምዳሜ ነው። በዘመን ጥፋት ዘንድሮን መቅጣት! እርግጥ ብዙኃን ኢትዮጵያውያን ዘውጋቸውን የሚያስቀድሙ ብሔረተኞች ሊሆኑ ይችላሉ። እኔንና መሰሎቼን ግን እነሱ ሸንጎ በሉት ጨፌ ውስጥ አስገድዶ የመክተት ወንጀል ነው። የራስን ማንነት በዘውግ ብሔር መግለጽ መብትም ምርጫም የሆነውን ያክል በኢትዮጵያዊነት መግለጽም ነውር ሊደረግ አይገባውም።

እኔን እንደ ምሳሌ

እኔ ባጋጣሚ ከተውጣጡ ብሔሮች ነው የተወለድኩት። ያደግኩትም ከዚያ በበለጠ አካባቢ በመጡ ቤተሰቦች መሐል ነው። የአብሮ አደግ ጎረቤቶቼ ቤተሰቦች ሙስሊም ጉራጌዎች፣ ወሎዬ ሙስሊሞች፣ ክርስቲያን የወለጋ ኦሮሞዎች፣ ትግሬዎች… ናቸው። ልጅ እያለን ማን "ምን" እንደሆነ ትዝ ብሎን አያውቅም። ስናድግ ግን ስለዘውግ ማንነቶቻችን እንድንማር ብቻ ሳይሆን አንዱን እንድንመርጥ ተገደድን። (መማሩን ወደን መገደዱን ግን ከመጥላት ሌላ አማራጭ የለንም።)

ሁሉንም በቅጡ አልችላቸውም እንጂ የአማርኛም፣ ኦሮምኛም፣ ሶማልኛም፣ ትግርኛም፣ ጉራግኛም… ዘፈኖች ስሰማ ባለሁበት በስሜት እወዘወዛለሁ፤ በፍቅር የምበላቸው ምግቦች (ኪሴ ሁሌም አይፈቅድልኝም እንጂ) ክትፎ፣ ጨጨብሳ፣ (እና በተውሶ ፒዛ እና በርገር ሳይቀሩ) ናቸው። አክሱም፣ ላሊበላ፣ ጅማ፣ ጎንደር፣ ሐረርን የጎበኘሁት እና ሌሎችንም ልጎበኝ ቀናት የምቆጥረው የራሴ የሚል ውስጣዊ ስሜት ስላለኝ ነው። ለጉዞ ስወጣ "የእነርሱን ልጎብኝ" አልልም፤ "የአገሬን ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ቅርሶች ልጎብኝ" ብዬ ነው። ከኢትዮጵያ መውጣት የማልፈልገው እንደኢትዮጵያ የሚመጥነኝ እና የምመጥነው (fit የማደርግበት) ስፍራ እንደሌለኝ ስለማምን ነው። ልዩነታችን ጌጤ ነው። እኔ የሁሉም፣ ሁሉም የኔ ናቸው ብዬ ከልቤ አምናለሁ።

Friday, February 7, 2014

“የደወሉላቸውን ደንበኛ ማግኘት አይችሉም"

የኢትዮ-ቴሌኮሟ ቅርፀ-ድምፅ ከመቼውም ጊዜ በላይ ሰሞኑን "የደወሉላቸውን ደንበኛ አሁን ማግኘት አይችሉም" ትላለች። ዛሬ (ጥር 29/2006) ግን ማለዳውን ሙሉ ስልኮች ሁሉ "ዝም፣ ጭጭ" ብለው ነው ያረፈዱት። አዲስ አበባን ከስሪ-ጂ (ሦስተኛው ትውልድ የስልክ በይነመረብ ግንኙነት አቅም) ወደ ፎር-ጂ (አራተኛው ትውልድ አቅም) ለማሳደግ፣ ሌሎቹን ክልሎች ደግሞ ወደ ሦስት ትውልድ ለማሳደግ ሥራዎች እየተጣደፉ እንደሆነ በሚደሰኮርበት በዚህ ሰዓት ኔትዎርኩ እንደ ክሪስማስ ዛፍ ብልጭ ድርግም ይል ገብቷል።

በነገራችን ላይ እኛ 1·1% የኢንተርኔት ፔኔትሬሽን (ተዳራሽነት) ላይ ቁጭ ብለን 28% ደረስኩ ብላ እንቁልልጭ የምትለን ኬንያ፣ በሁሉም ቴሌኮም ድርጅቶቿ የሚቀርቡት የስልክ አገልግሎቶች ከ3ጂ በላይ ናቸው። (Keeping up with the Joneses has become mission impossible).

ምትሐተ-ኢትዮቴሌኮም

ዛሬ የገጠመኝ ደግሞ ለየት ይላል። ሌላ ሰው'ጋ እደውላለሁ ብዬ አብሮኝ ያለው ሰው'ጋ ደወልኩ፤ ቢጠራም አይነሳም። ምንድን ነው ነገሩ ብዬ ስመለከተው የደወልኩት አብሮኝ ያለው ሰው'ጋ ነው።  "እንዴ የደወልኩት ላንተ ነው፤ አንተ ደግሞ አይሰማህም እንዴ?" ብዬ ሌላኛው ስልክ ላይ መደወሌን ቀጠልኩ። እሱ ደግሞ ኧረ እኔ'ጋ አልደወልክም ብሎ ስልኩን ሲያሳየኝ እኔ ከሌላኛው ሰው'ጋ ማውራት ጀምሬ ነበር። ከዚያ አብሮኝ ያለው ሰው የስልኩን ስክሪን ዓይኔ ላይ አምጥቶ ደቀነው። "befeqe is calling..." ይላል። "ኧረ እኔ ከሌላ ሰው'ጋ እያወራሁ ነው!" አብሮኝ ያለው ሰው ስልኩን ሊያነሳ ሲሞክር እምቢ አለው። ሁኔታውን 'ምትሐተ-ኢትዮቴሌኮም' ብለነዋል።

Wednesday, February 5, 2014

ተቋማዊ አምባገነን




አምባገነን መንግሥታት ሁሉ አንድ አይደሉም:: አንዳንዶች ፍጹም አውቶክራቲክ የሆነ አስተዳደር ሲኖራቸው ሌሎቹ ደግሞዴሞክራቲክየሚመስሉ ተቋማትን በመመስረት አምባገነንነት በመንግሥታዊ አስተዳደሩ ብቻ ሳይወሰን ተቋማዊ (Institutionalized dictatorship) ይዘት እንዲኖረው ያደርጋሉ:: በእነዚህ ተቋማት ውስጥ አምባገነኖች በሥራ ላይ የሚያውሏቸው ሁለት ዋና ዋና መሣሪያዎች አሏቸው፦ ጥቅማጥቅሞችን (ኪራይ) ማካፈል እና የጥቅም ተጋሪዎች ለሆኑት ሰዎች ጊዜያዊ የፖሊሲ ማስተካከያ (Policy concession) እና የአሰራር ሂድት ለውጥ በማድረግ ጥቅማቸውን ማስከበር ናቸው::

እነዚህም በትምህርት፣ በፋይናንስ፣ በኢኮኖሚ እና በመሳሰሉት ተቋማት ሲንጸባረቁ ይታያሉ:: አምባገነኖች እነዚህን ተቋዋማዊ አደረጃጀቶች የሚጠቀሙት ታቃዋሚን እና ተቃውሞን በስልታዊ መንገድ ለማርገብ ሲሆን ሂደቱ እንደ ተቃዋሚው ጥንካሬ ይወሰናል:: ለምሳሌ ተቃዋሚው ድካማ ከሆነ አምባገነኑ ጥቅሞችን በስፋት የማጋራት ግዴታ ስለሌበት ፖሊሲዎችን እና የውስጥ አስራሮችን ብቻ በመጠቀም ሥርዓቱን ያጠናክራል:: በተቃራኒው ተቃዋሚው ጠንካራ ከሆነ ደግሞ ጥቅማጥቅሞችን በማብዛትና ፖሊሲዎች ላይ ጊዜያዊ ለውጥ በማድረግ ተቃዋሚው እንዳያምጽ በሩን ይዘጋል (assurance for non-rebellion opposition):: ተቃዋሚው ደግሞ በጣም ጠንካራ ከሆነና የአምባገነኑን መንግስት ለመጣል የሚያበቃ ኃይል እና እድል እንዳለው የሚያረጋግጥ መረጃ ካለ ስርዓቱ ከጥቅማጥቅሞችን እና ከጊዜያዊ የፖሊሲ ለውጦች በተጨማሪ ሌሎች የመፍትሄ አማራጮችን ያቀርባል::

አምባገነን መንግሥት ተቃውሟቸውን በይፋ የሚገልጡ እና ጠንካራ ተጽዕኖ ሊፈጥሩ ይችላሉ የሚላቸው ላይ ትኩረት መስጠትና ጫና ማድረግ ይመርጣል:: ጫናውን በቀጥታም ሆነ በተዛዋዋሪ መንገድ ያድረገዋል :: ዋነኛው መንገድ ከላይ በተጠቀሱት መንገዶች በራሱ ቁጥጥር ውስጥ ካሉ ተቋማት በተለያየ መንገድ (systematically) ማስወገድ እና ከደረጃ ዝቅ ማድረግ ሲሆን ሌላው ደግሞ መወንጀል ማሰር ፣ማስፈራራት እና ከአገር እንዲሰደዱ ማድረግ ነው::

የስርዓቱ ተጠቃሚዎች የሚጠቀሙባቸው መንገዶች ለምሳሌ ያህል፦

የፎቶ ኤግዚቢሽን

ፎቶዎች ከቃላት በላይ ይናገራሉ እንዲሉ ባለፈው ዓመት ወዲያ ወዲህ ስል መንገዴ ላይ አጋጥመውኝ ካነሳኋቸው ፎቶዎች ላካፍላችሁ ወደድኩ:: እነሆ:-

አራት ኪሎ የፈረሱት ሰፈር አካባቢ ነው:: ጽሑፉ "ስለቀኑብን አፈረሱብን" ይላል:: ይህን ፎቶ ያነሳሁት አምና ነው:: አሁን በቀይ ቀለም ተሰርዟል::

ድርጅቱ በመስተንግዷቸው ከምናደንቃቸው አንዱ ቡና ሻጭ ካፌ ነው::

ከኢምፔሪያል ሆቴል ወደቦሌ ለመሄድ አንዳንዴ ከመኪና ይልቅ በጀልባ ይቀላል::


ፒያሳ - ራስ መኮንን ግርጌ


የቴኒክ ብልሽት:-  መጽሔቱ በአንድ እትሙ ሽፋን ገጹ ላይ ኢትዮጵያ ከስንዴ ኢምፖርት አድራጊነት አልተላቀቀችም ይላል፡፡ የውስጥ ገጹን ጽሑፍ ደግሞ በቀጣዩ ምስል ይመልከቱ፡፡
የቴኒክ ብልሽት (ቀጣይ):-  መጽሔቱ በውስጥ ገጹ ላይ ኢትዮጵያ ከስንዴ ኤክስፖርት አድራጊነት አልተላቀቀችም ይላል፡፡ (የሽፋን ገጹን ጽሑፍ ከላይ ይመልከቱ፡፡)




Not Yet Arrived in 2014. In front of Bole Friendship Building


ሁሉም ሰዎች አንድ ጋዜጣ (ልዕልና ከመታገዱ በፊት) - አሁን እነዚህ ካፌዎች በረንዳቸው ላይ አገልግሎት እንዳይሰጡ ታግደዋል::


ይህ ማስታውቂያ ተዘቅዝቆ ነው ወይስ ተልጦ ወይስ ግራ ቀኝ ተዛውሮ ወይስ ሁሉም? (ራስ መኮንን አለፍ ብሎ)


የቤተልሔም ሕንፃ /መገናኛ/ (ጀርባ - ፊቱን ከታች ይመልከቱ)
ቤተልሔም ሕንፃ ከፊቱ (በነገራችን ላይ ይህ ሕንፃ መስታወቱ አንፀባራቂ በመሆኑ እንዲቀየር ማስጠንቀቂያ ከተጻፈበት ወራት አልፈዋል::)
Guess Where? You got it right; it is in front of Bole Medhanialem - የጄኔራሎቹ ሰፈር
ለልማቱ ነው - ምናለበት?



ቃሊቲ (የጠጠር ማምረቻውን ስም ሳየው ያስቀኛል:: አንድ ሰሞን
ሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅን ድንጋይ ማምረቻ ይሉት የነበረው ይመጣብኛል፡፡)
Got it Wrong: የኮሌጁ የመጽሔት ማስታወቂያ ኮሌጅ የሚለውን ጠንቅቆ አልጻፈውም!

"ኢ-ልማታዊ መጽሐፎች" (ግልጽ በሆነ ምክንያት የትምህርት ቤቱን ስም ከመጥቀስ እታቀባለሁ)

"የልማት መስዋዕት" - ለገሃር ከለታት አንድ ቀን

Legend making: ቦሌ ቴሌ

ሶኒክ ስክሪን - ፒያሣ

Legend Making: ቦሌ - ሰን በርድ ካፌ (አሁን ጀግና አይሞትም የሚለው ቅርጽ ተነስቷል)

ሐዋሳ አውቶቡስ ተራ - "ከኤድስ ለማምለጥ በየሱስ ማመን ነው" Really?!

ሻሸመኔ - "የረዳኝ እግዚአብሔር ነው መኝታ ቤት" (ይህን ሳየው "እህቴ የላክሽልኝን ገንዘብ ቁም ነገር ላይ አዋልኩት ሬስቶራንት" ብሎ አብርሃም አስመላሽ የቀለደው ቀልድ ይታወሰኛል::)