Pages

Saturday, March 29, 2014

ኢሕአዴግን እንበይነው!

ሁሉንም ተቃዋሚ እንደአንድ መመልከትም ሆነ በአንድ አዕምሮ እንዲያስብ መጠበቅ የገዢው፣ የተገዢዎች፣ የተቃዋሚዎች ሁሉ የጋራ ችግር ነው። ሚሊዮን ችግሮች እና ሚሊዮን ተቃዋሚዎች ባሉበት አገር ውስጥ ተቃዋሚዎች ሁሉ አንድ ዓይነት ሊሆኑ አይችሉም። ይሁን እንጂ ሁሉም ተቃዋሚዎች ልዩነታቸውን በቅጡ ያውቃሉ ብሎ ለማለትም ያስቸግራል፤ ምክንያቱም “በስመ ተቃዋሚ ሲሳሳሙ" ማየት የተለመደ ነው። ተቃዋሚዎችን በተቃውሞ አካሔዳቸው መግባባት ላይ መድረስ እንዲያቅታቸው ከሚያደርጋቸው ችግር አንዱ ኢሕአዴግን የሚበይኑበት (define የሚያደርጉበት) መንገድ መለያየቱ ወይም ግልጽነት ማጣቱ መሆኑ የአደባባይ ምስጢር ነው።

ብያኔ ለምን ያስፈልጋል?

40 ዓመት ወደኋላ መለስ ብለን የአብዮቱን ልጆች ለመከፋፈል እና ለእርስበርስ እልቂት የዳረጋቸው ዋነኛውን፣ የሚታገሉትን አካል (ደርግን) የበየኑበት መንገድ ነው። የኢሕአፓ እና የመኢሶን ዋነኛ ልዩነት፣ የኢሕአፓና አንጃ እያለ የሚጠራቸው አባላቱ መካከል የተከሰተው የሐሳብ መሰነጣጠቅ፣ ብሎም እርስበርስ መጨራረስ ደርግን የሚበይኑበት መንገድ መለያየትን ተከትሎ የተወለደው ደርግን ለማስወገድ የመረጡት መንገድ ነው። ሁለቱ (የተቀናቃኝ ወገን ብያኔ እና የመቀናቀኛ መንገድ ምርጫ) ተሰናስለው የሚኖሩ ጉዳዮች ናቸው። በጥንቃቄ ሳይጤን የሚገበቡበት ገደል አይደለም።

ኢሕአዴግ፣ በዚህ ረገድ ራሱን ግልጽ የማድረግ ችግር የለበትም። ተቀናቃኞቹን አንዱን አሸባሪ፣ አንዱን የአሸባሪ ደጋፊ፣ ሌላውን ለዘብተኛ እያለ የሚኮረኩምበትን መንገድ አስቀምጧል። ኢሕአዴግ መሣሪያ ታጣቂ እንደመሆኑ ተቀናቃኞቹን ባይበይናቸውም ቅሉ ማሽመድመጃ መንገድ አይቸግረውም። ለተቃዋሚዎች ግን ‘ኢሕአዴግ ምንድን ነው?’ የሚለውን ጥያቄ መመለስ የሕልውና ጉዳይ ብቻም ሳይሆን ወዴት እና እንዴት እየሄደ እንደሆነ የሚያውቁበት ወሳኝ ጥያቄ ነው።

የበኩር ጥያቄ፤ ኢሕአዴግ ምን ያስባል?

Monday, March 24, 2014

‘Blame the Victim’: The Quest for Freedom vs. Professionalism of Media in Ethiopia?



16th of March 2014 marks the 1000th day since Reeyot Alemu, a newspaper columnist and teacher, was arrested for working to ethiopianreview.com news website which the Ethiopian State/court called ‘supporting terrorism’. On the same day, a twitter discussion focused on what happened to weaken the Ethiopian Press. Soleyana Shimeles, an activist for human rights and constitutional order, commented that the State ‘blames the victim after deliberately weakened the Press’. However, a twitter discussion following her tweet revealed that it is not only the State that blames the victim. Many ‘activists’ do. 


A Short Story of the Press

It is the same regime, the current regime, which created the Free Press and then tried to kill it. It is not dead yet; but it is also hardly possible to say it is alive. Researchers (Terje and Hallelujah, 2009) put the history of the Free Press in the past two decades in three overlapping periods:  

“…Tafari and others draw three periods of the private press in Ethiopia. The first period was the chaotic period from 1991 to 1997 with a blooming of new newspapers and anarchy journalism. The second period, 1997-2005 saw the establishment of professionally and ethically integrated newspapers like Reporter, Addis Admas, Fortune and Capital. The last period goes from 2005 when press freedom again came under threat after editors and journalists were imprisoned and persecuted after alleged transgressions following the May 2005 elections…” 

If the paper, from which the above excerpt was taken, was written now there would be a fourth period too – we may call it a counter-attack period! The current Press, however is mostly led by different people from the media leaders who existed pre-2005, it is now trying to counter attack (in becoming too critical of the State in its own way) past the self-defense time that followed its threat after the contested election in 2005.


Elections have become nightmares of the independent media. Even though the Press tried to recover from its wound of post 2005 election, the Ethiopian State planned to narrow the sphere to clear way for the 2010 election: the penal code was revised in relation to Free Press issues; the anti-terrorism bill, which clearly puts Freedom of Expression in danger, passed; the highly emerging Addis Neger newspaper journalists were intimidated to have eventually exiled; other journalists and bloggers were prosecuted in relation to terrorism; a few media houses such as Addis Admass took measures to toned down choosing existence over professional integrity. 

Saturday, March 15, 2014

የትግራይ ሕዝብ ከሕወሓት የተሻለ “ወዳጅ" አለው?

ከዚህ በፊት 'የትግራይ ሕዝብና ሕወሓት ምንና ምን ናቸው?' ብዬ በጠየቅኩበት ጽሑፌ፤ እጅና ጓንት ናቸው ብዬ ነበር። ስለብዙኃኑ ትግራዋዮች እያወራን ከሆነ አሁንም ያው ነው መልሴ። በዚያ ጽሑፍ እዚህ ድምዳሜ ላይ የደረስኩት ሕወሓት በሚያገኘው ሙሉ ድምፅ አይደለም፤ ያንን የሚያክል ድምፅ አዲስ አበባ ውስጥም የትም ፈጭቶ የትም አግኝቶታል። ሕወሓትን የሚወዱት አማራጭ አጥተው ነው ብዬ ነበር የተከራከርኩት። ምክንያቱም ደግሞ ትግራዋይ ያልሆነው ሰው ሁሉ ትግራዋዩን በሕወሓት መነፅር ስለሚመለከተው ተገፍቶ ነው ባይ ነበርኩ በዚያ ጽሑፍ (በዚህ ጽሑፍ ደግሞ 'ምን ዓይነት አማራጭ አጥቶ ነው?' የሚለውን ነው የምጠይቀው)።

እርግጥ ይሄ ብቻ በቂ ምክንያት አይደለም። ሕወሓት ለሁለት ዐሥርት ዓመታት የዘራው የጥርጣሬ ፕሮፓጋንዳ ትግራዋዮች ሕወሓትን ባይወዱት እንኳ ለሌሎች የሚኖራቸው ጥርጣሬ ከሱ ጉያ እንዳይወጡ ያስገድዳቸዋል። (ፀረ-ቅኝግዛት ተንታኞች የጥገኝነት አባዜ የሚሉት ዓይነት።)
ይህንን ድምዳሜ የእነአብርሃ ደስታን የግለሰብ እና አረና ፓርቲን የቡድን ቁርጠኛ ትግል አጣቅሶ ፉርሽ ለማድረግ የሚሞክር አይጠፋም ብዬ እገምታለሁ። ችግሩ፣ የአረና ተቀባይነት ከጥቂት የልሒቃን ትግራዋዮች አልፎ ብዙኃኑ ውስጥ ሰርጿል ወይ የሚለው ጥያቄ ሲመጣ ነው።

ወደ ጽሑፌ ርዕስ ስመለስ 'ወዳጅ' የሚለውን ቃል የተጠቀምኩበት ሕዝቡ የሚወደው ለማለት እንጂ ድርጅቱ የሚወደው ለማለት አይደለም። የአንድ ወገን ፍቅር ነው። አዎ፣ ሕዝብ ሆነን ስናስበው ሕዝቡ የሚወደው "የተሻለ" አማራጭ የለውም።