Pages

Thursday, August 18, 2011

የሁለት እምነቶች ጦርነት… [ወግ አጥባቂዎች እንዲያነቡት የማይመከር - ክፍል ሁለት]

በክፍል አንድ ጽሁፌ የፈጣሪ ሕልውናን በተመለከተ መከራከር እና የግል አቋም መያዝ እንጂ መደምደሚያ ላይ መድረስ እንደማይቻልና በሳይንሳዊ ሙግት የፈጣሪን ሕልውና (የቅዱሳን መጽሃፍትን ፍፅምና) ማረጋገጥ እንደማይቻል በጥቂት ነጥቦች መግለፄ ይታወሳል፡፡ ዛሬ ደግሞ ቃል በገባሁት መሰረት ጥቂት ስለዝግመተ ለውጥ እና ኢ-አማኒነት ለመነጋገር የሚያስችሉንን ነጥቦች ይዤ ቀርቤያለሁ፡፡

ጥቂት ስለዝግመተ ለውጥ
በዝግመተ ለውጥ (evolution) እሳቤ ላይ ብዙ ተሳልቆዎች ተነግረዋል፡፡ አብዛኛዎቹ ስላቆች የተነገሩት ባላዋቂነት መሆኑ ጥርጥር የለውም፡፡ ከቀልዶቹ መካከል አንዱን አንስተን ጥቂት እንነጋገርበት፡፡ አባትና ልጅ እያወሩ ነው፡፡
ልጅ፡- አባዬ፤ ሰው ከየት ነው የመጣው?
አባት፡- እኛማ የአምላክ ፍጡሮች ነን፤
ልጅ፡- አስተማሪያችን ግን ሰው ከዝንጀሮ ነው የመጣው ብሎ ነገረን፤
አባት፡- እንግዲህ እሱ አባቱ ዝንጀሮ ይሆናል፤ እኔና አንተ ግን የአምላክ ፍጡሮች ነን፡፡

ቀልዱ ሊያስቅ ይችል ይሆናል እንጂ መሰረታዊ ችግር አለበት፡፡ ምክንያቱም የዝግመተ ለውጥ እሳቤ ሰው ከዝንጀሮ መጣ አይልም፡፡ የዘንድሮ ሰው እና የዘንድሮ ዝንጀሮ አንድ ዓይነት የዘርግንድ ነበራቸው የሚል መላምታዊ ድምዳሜ ግን ያስቀምጣል፡፡ ይሄ እንዴት ሊሆን ይችላል - ወደ መልሱ የሚያመራን ጥያቄ ነው፡፡

Monday, August 15, 2011

የሁለት እምነቶች ጦርነት… [ወግ አጥባቂዎች እንዲያነቡት የማይመከር]

ዓለማውያን በምክንያት ሲሟገቱ ኢትዮጵያውያን ግን ገና ‹‹የዘራፍ›› ዘመን ላይ ነን፡፡ ይህንን ለመናገር ያደፋፈረኝ በሃይማኖታዊ ጉዳዮች ላይ ትችት መሰንዘር - በሃገራችን - ቡጢ የሚያስቀምስ ሃጢያት መሆኑን ስለማውቅ ነው፡፡ እኔ ኢ-አማኒ (atheist) ነኝ፡፡ በርግጥ እንደ ብዙሐኑ ሁሉ እኔም ቤተሰቦቼ በውልደት ያወረሱኝ አምልኮታዊ አስተሳሰብ ነበረኝ፡፡ ልዩነቱ ለአቅመ መጠየቅ ስደርስ የተነገረኝን መቀበል ስላልተቻለኝ የሆንኩትን ሆኛለሁ፡፡

ዛሬ በዚህ ጽሁፍ ላይ ትልቁ አጀንዳ የኔ ጉዳይ አይደለም፡፡ በርግጥ እኔ ኢ-አማኒ መሆኔን መግለፅ ያስፈለገኝ - ኢ-አማኒነት ከአማኒነት የተሻለ ምክንያታዊ ነው ብዬ ስለምከራከር ነው፡፡ ማንም አንባቢ ጽሁፌ ላይ የሚመለከተውን ሐሳባዊ ወይም አመክንዮአዊ ግድፈት በአስተያየቱ ሊጠቁመኝ ወይም በትችት ሊያር’ቀኝ (ር ይጠብቃል) የመሞከር መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ፈጣሪ አለ ወይስ የለም?

Saturday, August 6, 2011

ለመደገፍ መደገፍ፤ ለመቃወም መቃወም

ቲፎዞነት የጋርዮሽ ስርዓትን ይመስለኛል፡፡ ሰዎች በቡድን ሆነው አንድን ነገር ብቻ በፍጹም ልቦና ለመደገፍ የመቁርባቸው ነገር - ካሰቡት ያስቃል፡፡ ሰዉ ሁሉ በየፊናው የሚደግፈው የእግር ኳስ ቡድን፣ የፖለቲካ ቡድን፣ የሃይማኖት ቡድን፣ የፆታ ቡድን ራሱ ሳይቀር ያበጃል፡፡
ማንቸስተር ዩናይትድ (ብልጫ አወዛጋቢ ቢሆንም) በጨዋታ ብልጫ አርሴናልን ቢረታ እንኳን የአርሴናል ደጋፊዎች ‹‹በጨዋታ በልጠናል›› ብለው መሟገታቸው፣ ወይም ደግሞ የቡና ደጋፊዎች ‹‹ጊዮርጊስ ከፍሏል›› ማለታቸውን አያቆሙም፡፡

የኢሕአዴግ ደጋፊዎች ኢሕአዴግ የፈለገውን ያክል የሚያስቀይም አዋጅ ቢያወጣና ርምጃ ቢወስድ ‹‹ትክክል ነው›› ብለው ሽንጣቸውን ገትረው ከመሟገት አይመለሱም፡፡ የተቃዋሚዎቹም ቡድን እንዲያው ነው፡፡ በእያንዳንዷ የገዢው ፓርቲ ርምጃ ላይ የትችት እና ተቃውሞ በትራቸውን ከማሳረፍ አይመለሱም፡፡ (እሺ - አንመለሰም ካላልኩኝ ራሴን ማፅደቄ ነው፡፡) ከቡድኖቹ ቁማር ጀርባ ያለችውን ሃገር ማሰብም ያስፈልጋል::