Pages

Sunday, April 29, 2012

ከአከሌን አሰሩት እስከ አከሌን አገዱት!

From አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

ሰሞኑን ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ የተሰኘ እና መቀመጫውን ሰሜን አሜሪካ ያደረገ ቡድን ባጋለጠው መረጃ መሰረት INSA (Infromation Network Security Agency) በመባል የሚታወቀው መንግስታዊ ድርጅት ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር የ‹‹ተጠርጣሪ›› ግለሰቦችን ንግግር በመጥለፍ ሲያዳምጥ እና ሲቀዳ ይውላል ይለናል፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ምን እንደተከሰተ ባይታወቅም ይኸው INSA ከዚህ በፊት ከነበረው ትጋት በበለጠ በአንድ ሳምንት ብቻ ከመቶ በላይ ድረአምባዎችን እና ጦማሮችን አግዷል፡፡

የጦማር እገዳው ዘመቻ ጠንካራ ከመሆኑ የተነሳ አንዳንድ ጦማሪዎች ሲዘጋባቸው፣ አዲስ ሲከፍቱ፤ ሲዘጋባቸው፣ አዲስ ሲከፍቱ ሰንብተዋል፡፡ በፖለቲካዊ ሽሙጦቹ መንግስትን የሚያንጰረጵረው አቤ ቶክቻው (ይህንን ጽሁፍ እስከጻፍኩበት ጊዜ ድረስ ብቻ) ሰባት ጦማሮችን በመክፈት ክብረወሰን ለመስበር በቅቷል፡፡

Monday, April 23, 2012

የኢትዮጵያ መንግስት መጠላቱን የሚያሳብቁ ምልክቶች

From አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

እንደግለሰብ የምንጠላቸውን እንጂ የሚጠሉንን የማወቅ ዕድላችን ጠባብ ነው፡፡ እንደመንግስት ግን ጠባብ አይደለም፤ ሆኖም መንግስታቱ አምባገነን ከሆኑ በዙሪያቸው ያሉ ሰዎች ጥላቻቸውን የሚገልጹበት ድፍረት አያገኙም ስለዚህ እንደተጠሉ ላያውቁ ይችላሉ የሚል የግል ስጋት አለኝ፡፡ ፊደል ካስትሮ በስልጣናቸው ዘመን፣ በሕይወት ታሪካቸው ላይ የተሰራውን ፊልም ሕዝቡ በምን ዓይነት የፍቅር ስሜት እንደሚመለከተው ለማየት ራሳቸውን ቀይረው ሲኒማ ቤት ገቡ አሉ፡፡ እናም ገና ፊልሙ እንደጀመረ የፊደል ካስትሮ ፊት መታየት ሲጀምር ተመልካቹ በሙሉ ቆሞ አጨበጨበ፡፡ እርሳቸው በደስታ እየፈነደቁ ፀጥ አሉ፡፡ ታዲያ ከጎናቸው ተቀምጦ የነበረው፣ ‹‹አንተ፤ እየተነሳህ አጨብጭብ እንጂ! ካድሬዎቹ ያዩሃል’ኮ›› አላቸው ይባላል፡፡ ስለዚህ የኛዎቹም ይህ ዓይነት ቅዠት ውስጥ ሊሆኑ ስለሚችሉ÷ ሕዝብ እንደጠላቸው የሚያሳብቁ አንዳንድ ነገሮችን እናስታውሳቸው፡፡

Friday, April 20, 2012

ደጉ ኢትዮጵያዊ፤ ከልብ ካለቀሱ እምባ እንደማይገድ ያስመሰከረ ስብስብ


የዓለም ደቻሳ ልጆች፣ ባለቤት (መሃል) እና ወንድም (በስተቀኝ)
“አለቀለት ሲባል ፍቅር ተሙዋጠጠ
የፌስ ቡክ ዝምድና ነገርን ለወጠ::” ~ Bizu Hiwot
 
“ፌስን ቡክ አድርገው የተቀጣጠሩ
በልብ መነጽር ገጹን ያነበቡ
ሸበሌ ከትመው ታሪክ አስከተቡ፡፡” ~ Desu Aragaw
 
እነዚህ ግጥሞች የተገጠሙት ‹ደጉ ኢትዮጵያዊ› ላዘጋጀው የዓለም ደቻሳ ቤተሰብ ገቢ ማሰባሰቢያ የስነጽሁፍ ምሽት ለተገኘው የመጀመሪያ ስኬት፣ በፌስቡክ ላይ ነው፡፡ ወደስኬቱ በኋላ ላይ የምንመለስበት ቢሆንም መጀመሪያ ‹ደጉ ኢትዮጵያዊ› ምንድን ነው፣ ማነው፣ ከየት ነው፣ ወዴት ነው? የሚሉትን ጥያቄዎች በአጭሩ እንመልስ፡፡
 
‹ደጉ ኢትዮጵያዊ› ከዚህ በፊት በአካል የማይተዋወቁ 16 የፌስቡክ ጓደኛሞች የፈጠሩት የፌስቡክ ቡድን ነው፡፡ የደጉ ሳምራዊን ታሪክ መነሻ አድርጎ÷ በሊባኖስ መንገድ ላይ እየተጎተተች መኪና ውስጥ እንደትገባ ከተደረገች በኋላ በማግስቱ ራሷን አጥፍታለች የተባለችውን ዓለም ደቻሳ ቤተሰቦች የእዝን ለመስጠት እና እግረ መንገዱንም ስለጉዳዩ አሳሳቢነት አነስተኛ ግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም ለማዘጋጀት የተመሰረተው ‹ደጉ ኢትዮጵያዊ› ምንም እንኳን ሕጋዊ ሰውነት የሌለው ቡድን ቢሆንም በበጎ ፈቃደኝነት መስራት የሚፈልጉትን መስራቾቹን እና በፌስቡክ በተከፈተው የቡድኑ ገጽ ውስጥ በገቡ ከ4,000 በላይ አባላቶቹ ድጋፍ የሚከተሉትን ዓላማዎች ግብ አድርጎ ለመንቀሳቀስ ሕልም አለው፡፡

Sunday, April 15, 2012

የቴዲ አፍሮን አልበም ያልገዛሁባቸው 5 ምክንያቶች

From አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

ባለፈው ሳምንት የቴዲ አፍሮን አልበም እንድንገዛ የሚያስገድዱንን 5 ምክንያቶች አንብቤ ነበር፤ አላሳመኑኝም እንጂ! ስለዚህ አልገዛሁም፡፡ ባልገዛም አዳምጬዋለሁ፡፡ በርግጥ ሳይወጣ በፊት ላለመግዛት መወሰኔ በራሱ፣ ከወጣ በኋላ ለምን አልገዛሁትም ብዬ የምናገረው ነገር ሰሚን ላይማርክ ይችላል ግን ምንአገባኝ፡፡ ግን ምናልባት ‹ገንዘብ ቸግሮት የቴዲን አልበም አልገዛም› ብለው የሚያሙኝን ሰዎች ዝም ለማሰኘት ምክንያቴን እደረድራለሁ፡፡ (በነገራችን ላይ ትላንት ከኢትዮፒካሊንክ እንደሰማሁት÷ ያቺ እንኳን የፕሬዚደንት ግርማ ወልደጊዮርገስን የሕይወት ታሪክ በዶኩመንተሪ እሰራለሁ ስትል የነበረችው አምለሰት ሙጪ ስንት ሳዱላዎች የተጋደሉለትን ቴዲን በእጇ አደረገችው ማለት ነው በቃ?)

Friday, April 6, 2012

እስኪ እንጠያየቅ፤ አገራችን የት ነው? (መጠባበቂያ ካስፈለገ)

From አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

ከመቶ ዓመት በፊት፣ በሃገራችን ሸንጎዎች የሚካሔዱት በተጻፈ ሕግ ሳይሆን በዳኞቹ የብልሐት ፍርድ ነበር፡፡ በምኒልክ ዘመን በዳኝነት ጥበባቸው ስማቸው ደጋግሞ የሚነሱት ፊታውራሪ ኃብተጊዮርጊስ ናቸው፡፡ ካልተሳሳትኩ - ከዳኝነት ባንዱ የሚከተለው የገጠማቸውም እርሳቸው ናቸው፤ አንድ ሕፃን ልጅ ‹የኔ ነው፣ የኔ ነው› በሚል የተካሰሱ ሁለት ሴቶች ፍርዳቸውን ሽተው ቀረቡ፡፡

ኃብተጊዮርጊስ በጣም ተጨንቀው፣ አውጥተው፣ አውርደው ውሳኔያቸውን አሳለፉ፡፡ “እንግዲህ ሁለታችሁም እናት ነኝ ብላችኋል፡፡ ሁለታችሁም እናት መሆናችሁን ምስክር አቅርባችሁ አረጋግጣችኋል፡፡ እኔም ሁለታችሁም እናት መሆናችሁን አምኛለሁ፡፡ ስለዚህ ልጁ ለሁለት ተሰንጥቆ እኩል፣ እኩል እንድትካፈሉት ፈርጃለሁ፤” ብለው ወሰኑ፡፡

ውሳኔው እንደተላለፈ፣ አንደኛዋ ሴት ብትስማማም ሌላኛዋ ግን “በቃ ይቅርብኝ፣ ልጄ አይደለም፤ ትውሰደው” አለች፡፡ ይሄን ጊዜ ኃብተጊዮርጊስ “ልጁን ለመካፈል የተስማማችውን ሴት እንድትቀጣ ፈርደው ሲያበቁ፣ በልጇ መጨከን አቅቷት ‹ልጄ አይደለም› ለማለት ለበቃችው ሴት የእናትነት መብቷን አጎናጽፈዋታል፡፡

ከመቶ ዓመት በኋላስ?

Sunday, April 1, 2012

መራመድና ባሉበት መሽከርከር፤ ሁለት የኑሮ ፈሊጦች

From አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

ወ/ሮ ሙሉ፤ የኢትዮጵያ ንግድ ማሕበራትና ሴክቶራል አሶሲየሽን ፕሬዚዳንት - ልምዳቸውን እያጋሩ ነው፡፡ “ጣጣ” በማያውቀው አማርኛቸው የተራመዱበትን የሕይወት መንገድ (ልበለው ስኬት) ያወራሉ፣ ያወራሉ፤ እኔም አዳምጣለሁ፣ አዳምጣለሁ፡፡ በመሃል ‘ከራስ ጋር መወዳደር’ ስለሚባል ነገር አነሱና ተናገሩ፡፡ “መወዳደር ያለብን ከሰዎች ጋር ሳይሆን ከራሳችን ጋር ነው፣ እከሌ እንዲህ ስለሆነ እኔም መሆን አለብኝ ማለት የለብንም” አሉ፡፡ ተቀየምኳቸውና እርሳቸው ጨርሰው ታዳሚው ጥያቄ እንዲጠይቅ ዕድል ሲሰጠው እጄን ዘለግ አድርጌ አወጣሁ፡፡

“አነጋገርሽን ወድጄልሻለሁ፤” ብዬ ጀመርኩ፡፡ በነገራችን ላይ ወይዘሮዋ፣ የአራት ልጆች እናት ቢሆኑም፣ የ33 ዓመት የሥራ ልምድ ቢኖራቸውም ዕድሜያቸውን 24 እያሉ ነው የሚናገሩት (energetic መሆናቸውን ለመግለፅ ይመስለኛል፤) እንዲያውም የ24 ዓመት ሰው እንዴት 33 ዓመት የሥራ ልምድ ይኖረዋል ሲባሉ÷ ቀሪው ‘over time’ የሰራሁት ነው ብለው መመለሳቸውን ነግረውናል፡፡ ለዚያ ነው እኔም አዳራሹ ውስጥ አንቺ ማለቴ፡፡ ስቀጥል፤