Pages

Friday, June 29, 2012

አምስት የኢትዮጵያ ጠላቶች

From Africa Ave, Addis Ababa, Ethiopia

‹‹ኢትዮጵያ አገሬ›› ከሚለው ሐረግ በቀር በዚህ ዘመን አንገት የሚያስቀና ነገር ማግኘት እየከበደ ነው፡፡ እሴቶቻችን እየተሸረሸሩ፣ ፍቅራችን እየጠወለገ፣ ተስፋችን እየመነመነ.. መጥቷል፡፡ መንስኤው እንደውጤቱ እልፍ ነው፡፡ እኔም እንደወትሮዬ አምስት አጀንዳዎችን አንስቼ አንድነታቸውን የማስደመድምበት ምክረ መጣጥፍ ይዤ ቀርቤያለሁ - እነሆ!

1ኛ
‹‹ገበታ ንጉሥ ነው››
ገበታ እንደንጉሥ የሚቆጠርባት ኢትዮጵያ ገበታን ለማግነን ምክንያት አላት፡፡ የዓለም ስልጣኔ እምብርት የሆነችው ግብጽ ጥንታዊና ዘመናዊ ከተሞቿ የተቆረቆሩት በአባይ ወንዝ ዳርቻ ነው፡፡ ግብጽ ምድሯ ውሃ ባያፈልቅም ከደጇ በሚያልፈው ውሃ ሕዝቦቿን ከረሃብ ለመታደግ ችላለች፡፡ ‹‹ከሞኝ ደጃፍ ምሳር ይቆረጣል›› ነውና ተረቱ ኢትዮጵያ ግን የረሃብ ምሳሌ ነች፡፡ ከሰማይ ዝናብ ዘነበ/አልዘነበ በሚል የምግብ ዋስትናዋን በሚትዮሮሎጂ ዕድል ላይ የጣለችው ኢትዮጵያ የረሃብን ነገር ታውቀዋለች እና ‹‹ገበታ ንጉሥ ነው›› እያለች ብትተርት አይፈረድባትም - ረሃብ አንደኛ ጠላቷ ነውና፡፡

2ኛ
‹‹ይታደሉታል እንጂ አይታገሉትም››
ኢትዮጵያውያን አማኞች ናቸው፡፡ ክርስትና ከመፈጠሩ በፊት አክሱም ሃውልትን ያስቆማቸው እምነታቸው ነው፡፡ ነገሮች ሁሉ በፈጣሪ ፈቃድ እንጂ በሰው ጉልበት ይሆናል ብለው አያምኑም፡፡ ይህንን በርካታ ምሳሌና የኑሮ ዘይቤያቸው ይመሰክራል፡፡ እርግጥ በዘመናዊዋ እና በቀድሞዋ ኢትዮጵያ መካከል ልዩነት ይኖራል ብሎ መጠርጠር መልካም ነው፡፡ እንደምሳሌም ጥንታዊዎቹ የአክሱም ሐውልትን ያቆሙት በትግል እንጂ በዕድል አይደለም፤ ሌላ ምሳሌ፣ ቀደምት የላሊበላ ታሪክ ጸሃፊዎች ላሊበላ የታነፀው እነዚህ ታሪክ ጸሃፊዎች የኢትዮጵያውያንን የእጅ ሥራ ‹‹ታድለው›› እንጂ ‹‹ታግለው›› ያገኙት ስላልመሰላቸው ከነዚያኞቹ እነዚህኞቹ ያንሳሉ - እምነትን በመምረጣቸው ብቻ ሳይሆን መታደልን ቁጭ ብለው በመጠበቃቸው፡፡

‹‹ጠንቋይ መቀለብ›› የተሰኘች አባባል አለች፤ ‹‹ማወቅን›› ትወክላለች፡፡ በአገራችን ‹አዋቂ› የሚለው ቃል ‹ጠንቋይ› ከሚለው እኩል ያገለግላል፡፡ የእጅ ሥራ ባለሙያዎች ጥሩ ስም የላቸውም - ‹‹ቡዳ›› ናቸው፡፡ አሁንም ድረስ በሥራው ግን በቶሎ የተሳካለት ሰው/ነጋዴ ‹‹ምን የተለየ ሥራ ሰርቶ ነው?›› ብሎ ሊማርበት ከሚፈልገው ይልቅ ‹‹አስጠንቁሎ/አስደግሞ ነው›› እያለ የሚያማው ተመልካች ይበዛል፡፡ ከሥራ ይልቅ ምትሃት ዋጋ አለው፡፡ ድህነቱንም ሮጦ ያመለጠ ሰው ግፋ ቢል ‹‹ፈጣሪ ረዳው›› ይባል እንደሆን እንጂ ‹‹ለፍቶ አገኘ›› የሚባልበት ጊዜ እምብዛም ነው፡፡ ኢትዮጵያ ችግር ላይ ነች - ዜጎቿ ለስኬት አቋራጭ መንገድ ያስሳሉ - አምልኮን ወይም እምነትን የሙጢኝ ብለው ‹‹የቆጡን ሲጠብቁ፣ የብብታቸው››ን ያጣሉ፡፡

3ኛ

Thursday, June 28, 2012

የተመቻቸ ጊዜ መጠበቅ?

From አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
ኅወሓትን ለ10 ዓመታት የመሩት አቦይ ስብሃት፣ የመሪነቱን ሥልጣን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በፈቃዳቸው ካስረከቡ 23 ዓመት ሆኗቸዋል፡፡ ለአዲስጉዳይ በሰጡት ቃለምልልስ ላይ፣ አቦይ ስብሃት ‹‹የኅወሓትም ሆነ የኢሕአዴግ ሕገ-ደንብ አንድ ኃላፊ በስልጣን ላይ የሚቆይበትን ዓመት አይገድብም፡፡…›› ብለው ተናግረዋል፡፡ እውነት ነው፤ እንኳን የፓርቲው የአገሪቱ ሕገ-መንግስትም ለ‹‹ትዕምርትነት›› የሚቀመጠውን ፕሬዚደንት የስልጣን ዘመን ሲገድብ፣ የክልል ፓርላማን እስከመበተን ስልጣን የተቸረውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዘመነ መንግስት አይወስነውም፡፡

ኢሕአዴግ እንዲህ ዓይነት ነገር ይወዳል፡፡ ለምሳሌ በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 39 ላይ ‹የራስን እድል በራስ መወሰን እስከመገንጠል› ብሎ ይጽፍና ‹መገንጠል›ን ምን አመጣው ተብሎ ሲጠየቅ ‹‹ብሔር ብሔረሰቦች በመፈቃቀር እና በመፈቃቀድ አብረው የሚኖሩት የመለያየት መብት እንዳላቸው ስንነግራቸው ነው›› ብሎ ይከራከራል፡፡ በዚህ ‹‹ሕገ-መንግስታዊ አተረጓጎም›› ነው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ዘመነ መንግስት አለመገደብን የምመለከተው፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትሩ (ወይም የኢሕአዴግ) የስልጣን ዘመን አለመገደቡ፣ አንድ፤ አቦይ ስብሃት እንዳሉት ‹‹…ፕሮግራሙን ማዕከል አድርጎ የጋራ አመራርን እስካረጋገጠ ድረስ…›› ችግር የለውም ለማለት ይመስላል፣ ሁለት፤ የስልጣን ዘመኑ ሳይገደብ በገዛ ፍቃዱ ይለቃል የሚል ተስፋ ይዞ ይሆናል - ልክ እንደመገንጠል/አለመገንጠሉ፡፡ ሦስት፤ የፓርቲው ሊቀመንበር ቁጭ ባሉበት የሊቀመንበሩ የሥልጣን ዘመን ይወሰን የሚል ጥያቄ ማንሳት ለአባላቱ አስፈርቷቸው ይሆናል፡፡

ስልጣንን መልቀቅ ለምን ያስፈልጋል (101)?

Saturday, June 23, 2012

Hookah እና አሜሪካ

From አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

ይህንን ጽሁፍ ለመጻፍ ስነሳ ‹‹የኛ ሰው በአሜሪካ›› የሚል ርዕስ ልሰጠው ፈልጌ ነበር፡፡ ችግሩ ይሄ ርዕስ አሜሪካንን ረግጠው በተመለሱ ሰዎች ስለተለመደ ባይተዋርነት ተስማምቶኝ ተውኩት፤ በሌላ በኩል የየኛ ሰው በአሜሪካ ኑሮ በሁካ ብቻ አይገለፅም የሚል ርህራሄም ተሰምቶኛል፡፡

ሁካ - የሺሻ አሜሪካዊ ስሟ ነው፡፡ አዲስ ጋይድ የምትባል፣ በቀለም የተንቆጠቆጠች፣ ዲዛይኗ እና ጠረኗ ያማረ፣ ጽሁፎቿ ዋዘኛ፣ ዳያስፖራውን ኢላማ ያደረገች መጽሄት በአጋጣሚ እጄ ገብታ ሳገለባብጣት ማስታወቂያ እንደሚበዛባት አስተውያለሁ፡፡

ካየሁዋቸው ማስታወቂያዎች ውስጥ - በተለይም የአበሻ ካፌና ሬስቶራንቶቹ ማስታወቂያዎች ከዘጠኙ ስምንቱ ሁካን በስዕል ወይም በጽሁፍ አስተዋውቀዋል፡፡

የሁካ ማጨሻዋ እቃ በወርቃማ ቀለም የተንቆጠቆጠ፣ ዙሪያው በአረቢያል መጅሪስ የደመቀ፣ አፋቸው ላይ ጡሩምባ መሳይ የሁካውን ጫፍ የሰኩ ወይም እንደፈላ ጀበና ከአፋቸው ጢስ ቡልቅ፣ ቡልቅ የሚያደርጉ ሴቶች፣ ወዘተ፣ ወዘተ ለቁርስ ቤቶቹ ማስታወቂያ ሳይቀር ፍጆታ ሁነዋል፡፡

‹‹የኛ ሰዎች በአሜሪካ›› ታሰቡኝ!

Sunday, June 17, 2012

እነአልበርት አይንስታይን ስለዘንድሮው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ምን ይላሉ?


ስም ያለው ነገር ሁሉ ‹‹ያለ›› ነገር ነው እያለ ከልጆቹ’ጋ ሲሟገት የነበረ አንድ ጦማሪ ወዳጄ፥ ስማቸው ከመቃብር በላይ የዋለላቸው ሰዎችም ስማቸውን የሚጠሩ ሰዎች እስካሉ ድረስ ‹‹የሉም›› ማለት አይቻልም - ምክንያቱም ‹‹አሉ›› ብሏል፡፡ መከራከሪያው ለዚህ ጽሁፍ መንደርደሪያ ግብአትነት ብቁ ስለሆነ ያለምንም ክርክር ተቀብዬዋለሁ፡፡ የጨዋታዬ ርዕሰ ጉዳይ ግን ‹‹ያለ›› እና ‹‹የሌለ›› ነገር አይደለም፡፡ ይልቁንም አንዳንድ ሕያዋን ሰዎች ከተናገሯቸው ሕያው ንግግሮች መካከል እያጣቀሱ የዛሬውን የአገራችንን ፖለቲካ መሄየስ ነው፡፡ በምናባዊ ሳይንስ ሊቁ አልበርት አይንስታይን ብንጀምርስ?

1. አልበርት አይንስታይን
“The world will not be destroyed by those who do evil, but by those who watch them without doing anything.” (ዓለማችን የምትጠፋው ክፉ በሚያደርጉ ሰዎች ሳይሆን ክፉ ሲያደርጉ እያዩ ዝም በሚሏቸው ሰዎች ነው፡፡)

በኢትዮጵያ የፖለቲካ እውነታ በየጓዳው ከመንሾካሾክ እና ከመብሸቅ ባሻገር ይሄ መንግስት (ይሄ ገዢ) ያለእኛ ተገዢነት እና ፈቃደኝነት ሊጨቁነን እንደማይችል ገብቶን የተነጠቅነውን ነፃነት ለማስመለስ የምንሞክር እጅግ ጥቂቶች ነን፡፡ በተለይም ‹‹ኢኮኖሚያዊ ዕድገቱ ብዙሐኑን ስላላማከለ አንድ ቀን አገሪቱ ወደማትወጣው ችግር ውስጥ ትገባለች፣ ወዘተ. ወዘተ...›› እያሉ የጋን ውስጥ ትንታኔያቸውን የሚሰጡት ነገር ግን ለጋዜጣ እንኳን ማብራሪያ ለመስጠት ‹‹ስሜ ከተጠቀሰ አይሆንም›› የሚሉ ምሁራን ከአጥፊው ገዢው ፓርቲ ይልቅ - ለጥፋቱ ተጠያቂ መሆናቸው አይቀሬ ነው፡፡

Monday, June 11, 2012

የአንድ ኪራይ ሰብሳቢ መንግስት ታሪክ

From አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

የመንግስት መሥሪያ ቤቶች እጣ ክፍሎቼ እንዳልሆኑ እየተረጋገጠ ነው፡፡ ባለፈው ሰሞን እርሜን ‹ኢሚግሬሽን› ብሄድ ለሦስት ሰዓታት በግዞት እንደቆየሁ አጫውቻችሁ ነበር፡፡ ዛሬ ጠዋት ደግሞ የጓደኛዬን ጉዳይ ላስፈጽም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሰነድ ማረጋገጫ ቢሮ ተገኘሁ፡፡ እዚህ እንደከዚህ ቀደሙ አካላዊ ጥቃት ባይደርስብኝም - መንግስታችንን በኪራይ ሰብሳቢነት እንድታዘበው የሚያደርገኝ ነገር ተከስቷል፡፡

ነገሩ ወዲህ ነው፡፡ የሰነድ ማረጋገጫ ሥራ የሚባለው ሰነዱን ባለቢሮዎቹ ተኮር ብለው ካዩት በኋላ ማሕተም ይመቱበታል - አለቀ፡፡ ይህ ሥራ የ30 ሰከንድ ሥራ ቢሆንም ብዙ ያስከፍላል - በጊዜም፣ በገንዘብም፡፡

እኔ የሄድኩት አንድ የትምህርት ማስረጃ ሰነድ ላይ የእውነተኛነት ማረጋገጫ ማሕተም ለማስመታት ነው፡፡ ይህንን ሰነድ ሌላ ቦታም ቀደም ብሎ ማረጋገጫ ማሕተም ማስመታት በቅድመ ሁኔታነት ተከናውኗል፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የሰነዶች ማረጋገጫ ቢሮ ደግሞ ከግቢ ውጪ ጥቂት፣ ጊቢ ውስጥ ደግሞ በአግዳሚ ወንበር እና ከዚያ የተረፈው ግድግዳ ተደግፎ ቆሞ የተሰለፈ ብዙ ሰው አለ፡፡ ያንን መጠበቅ - በተለይ እንደኔ ላለውና በስጋ ሳይሆን ባጥንት ብቻ ለቆመ ሰው - ወገብን ይፈታተናል፡፡

በግምት ለሁለት ሰዓታት ያህል በሰልፍ ጠብቄያለሁ፡፡ ተሰልፌ ግን ስሰጋ የነበረው ስለወገቤ፣ ስለጥበቃው ወይም ከምሳ ሰዓት በፊት ወረፋው ባይደርሰኝስ ስለሚለው አልነበረም፡፡ እነዚህኞቹ እዳቸው ገብስ ነው፡፡ እኔን የጨነቀኝ ይህን ሁሉ ሰዓት ጠብቄ ያላሟላኸው አንድ ነገር አለ ተብዬ ሰልፉን እንደገና እንድጀምር ብደረግስ?

Saturday, June 9, 2012

“አሸባሪ” ፊልምም ይታገድ ጀመር

From አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

ከዚህ ቀደም ‹የባሕር በር› በሚል ርዕስ በጥላሁን ጉግሳ የተሰራው የአማርኛ ፊልም በኢቴቪ ማስታወቂያው እንዳይታይ ታግዶ የአንድ ሰሞን አወዛጋቢ አጀንዳ ለመሆን በቅቶ ነበር፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የፊልሙ ዋና ገጸ ባሕሪ የሆኑት ፕሮፌሰር ‹‹በእኔ እምነት፣ ኢትዮጵያና ኤርትራ አንድ ቀን መልሰው አንድ ይሆናሉ፡፡›› ብለው መናገራቸው ነው፡፡ ያለምንም ማጋነን መለስ ዜናዊ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ አንድ ሆነው ከሚያዩ ከሚና ሕንጻ ላይ ዓይናቸው እያየ ቁልቁል ቢወረወሩ ይመርጣሉ፡፡ የሻዕቢያን የጫካ ውለታን ኤርትራን እንደተገነጠለች በማስቀረት ነው የሚያረጋግጡት፡፡ እንዴያውም አንዳንዴ ሳስበው መለስ ከስልጣን መውረድ የማይፈልጉት ለሻዕቢያ እንደርሳቸው ታማኝ የሚሆን ኢትዮጵያዊ መተካት ስለሚከብዳቸው ይመስለኛል፡፡

ወደቀደመው ነገራችን ስንመለስ ትላንት አርብ፣ በኤድናሞል ማቲ መልቲፕሌክስ ሲኒማ መታየት የጀመረው ‘The Dictator’ የተሰኘ ፊልም እንዳይታይ ታገደ የሚል ዜና አነበብኩ፡፡ መውጣቱን ከሰማሁ ጀምሮ በጉጉት ስጠብቀው የነበረው ይህ እምባና ሳቅ ያዘለ (comedy satire) ፊልም ሦስት ቀን እንኳን እንዳይታይ በመደረጉ ለእሁዴ ሳይደርስልኝ ቀርቷል፡፡ ግን ለምን የሚለው ጥያቄ አጭር ግምቴን እንደሚከተለው አስቀምጣለሁ፡፡  

በባሮን ኮኸን በገዛ ፊልሙ መሪ ተዋናይ የሆነበት ይህ ስላቃዊ ፊልም የጋዳፊ እና የሳዳም ሁሴን ድቅያ የሆነ አምባገነነዋ ገዢ ሆኖ የሚጫወት ገጸ ባሕሪ ፈጥሯል፡፡ ከፊልሙ ቅኝቶች ላይ ለማንበብ እንደሞከርኩት በርካታ የአምባገነኖች ባሕርያት የተሰገሰጉበት ይህ ፊልም፣ ከአንድ ወዳጄ እንደሰማሁት ደግሞ የኛውን ‹መለስ› ዜናዊን ቁልጭ የሚመስሉ በርካታ ትዕይንቶች አሉት፡፡ እናም የፊልሙ መታገድ ዋነኛ ምክንያት ከዚህ ውጪ ምን ሊሆን ይችላል?

በርካታ ጋዜጦች ታገዱ፣ ሰላማዊ ሰልፍ ታገደ፣ በመንግስት ያልተወደዱ ዘፈኖች በመንግስት ይዞታ ስር ባሉ ሬዲዮ ጣቢያዎች እንዳይተላለፉ ታገዱ፣ አንዳንድ መጽሃፍቶች ሜጋ መጽሃፍት ማከፋፈያ ውስጥ እንዳይገቡ ታገዱ፣ የተቃዋሚ ድረገጾችና ጦማሮች ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይነበቡ ታገዱ፣ የጀርመንና የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮዎች ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይሰሙ ታገዱ፣ …. ታገዱ፣ ታገዱ፡፡

እነዚህ ሁሉ ነገሮች መታገዳቸው የሚነግረን አንድ ነገር ብቻ ነው፡፡ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስቴር፣ ራሳቸውን ከነሞቡቱ፣ ሙአመር… (The ‘M’ Dictators) ሳይሆን ከነማንዴላ (The Democrats) ጋር ማመሳሰል ሲመኙ የነበሩት መለስ ዜናዊ፣ ሕዝባቸውን ነፃ ለማውጣት ትምህርታቸውን አቋርጠው “የነፃ አውጪ ትግል” የጀመሩት መለስ ዜናዊ፣ አምባገነንነታቸው ከተረጋገጠላቸውና የአምባገነንን መጨረሻ ከቀመሱት ሳዳም ሁሴን እና ሙአመር ጋዳፊ እንዳንዱ መሆናቸውን እርሳቸው ራሳቸውም ሆኑ የማገዱን ሥራ እየተከታተሉ የሚፈጽሙላቸው ተከታዮቻቸው ማመናቸውን ያረጋግጣል፡፡