Pages

Monday, July 25, 2011

በዻሳ ወይስ badhaasaa?

የብሔር ፖለቲካ በጣም ስስ (sensitive) ነው፡፡ በቀላሉ ተቆስቁሶ ብዙ ሊጓዝ ይችላል፡፡ ኢትዮጵያ በኢሕአዴግ ዘመን፣ በብሔር ፌዴራሊዝም ከተከፋፈለች ወዲህ እንኳን የብሔር ፍላጎቶችና ጥያቄዎች አጥጋቢ መልስ አላገኙም፡፡ የኦሮሞ ብሔረሰብ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ውስጥ ከ34 በመቶ በላይ ድርሻ አለው፡፡ (2007 National Census) ሆኖም የኦሮሞ ሕዝብ ለዘመናት የሚገባውን ትኩረት የመነፈጉ ጉዳይ ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ ለሚሆን ጊዜ ሲያነታርክ ቆይቷል፡፡

የብሔር (በተለይም የኦሮሞ ተወላጆች) ፖለቲካ ጉዳይ የታገሉለትን ያሕል ብዙ መሻሽል ባያስመዘግብም፣ በርካታ አማራጮችን ለፖለቲካው የሚመግቡ ኢትዮጵያውያንን አፍርቷል፤ እነ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ እነ ቡልቻ ደመቅሳ እና እነ ዶ/ር መረራ ጉዲና የዚህ ትሩፋቶች ናቸው፡፡

ለነገሩ የዚህ ወጌ ቁምነገር የብሔር ፖለቲካ በጥቅሉ አይደለም፤ ነገር ግን ከብሔር ፖለቲካ ዘውግ ውስጥ አንዱን መዝዤ መሟገት ቃጥቶኛል፡፡ ጉዳዩ የተቀበረ ቢመስልም ለኔ ግን ገና አልሞተም፤ ልክ በኤርትራ መገንጠል ጉዳይ ላይ መቁረጥ እንዳልቻልኩት ሁሉ - በዚህም ገና አልቆረጥኩም፡፡

በነገራችን ላይ ኢሕአዴግ ‹‹በመቃብሩ ላይ›› ካልሆነ በቀር የማይቀይራቸው በርካታ ጉዳዮች መካከል ይመደባል የዛሬ ጉዳዬ፡፡ ለዚያ ነው ብዙዎቹ ኢትዮጵያዊ ምኞቶቼ እውን እንዲሆኑ ቶሎ የኢሕአዴግ መቃብር እንዲማስ ሌት ተቀን የምመኘው፡፡

አላግባብ ልብ ማንጠልጠሌን ልተወውና

Friday, July 8, 2011

እንኳን ኢሕአዴግ ደርግም ወድቋል

ደርግ አንቀጥቅጦ በመግዛት አቻ የለውም፡፡ የሰራዊቱ ግዝፈት እንኳን ተራ ሽፍቶች የተደራጀ ጦር እንኳን የሚደመስሰው አይመስልም ነበር፡፡ የሰራዊት ግዝፈት ለአንድ ስርዓት ዋስትና ሊሆን እንደማይችል የተረጋገጠው በደርግ ውድቀት ነው፡፡

ለደርግ መውደቅ የራሱ የሰራዊቱ አስተዋፅዖ ቢኖርበትም እምነት አጉዳዩ የደህንነት ቢሮ ትልቅ ሚና ተጫውቷል፡፡ በወታደራዊ ስልት እዚህ ግባ የማይባል ዕውቀት የሌላቸውብሶት የወለዳቸውሽምቅ ተዋጊዎች ዘመናዊ አደረጃጀት ያለውን ግዙፉን ወታደራዊ መንግስት የገረሰሱት በዚህ ምክንያት ነው፡፡

Saturday, July 2, 2011

የመለስ ፖለቲካ እና የኢትዮጵያ አበሳ ባሳለፍነው 20 ዓመት

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢትዮጵያ መንግስት፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ምናምን ማለት እየደበረኝ ነው፡፡ ምክንያቱም ለ20 ዓመታት ሲገዙ የነበሩት አቶ መለስ ዜናዊ የሁሉም ነገር ፈጣሪና ፈላጭ ቆራጭ ናቸው፡፡ ስለዚህ የኢትዮጵያ ከተባለ እኛንም ስለሚወክል፤ የመለስ ማለትን መርጫለሁ፡፡ “Power corrupts; absolute power corrupts absolutely” (ስልጣን ያበላሻል፤ ፍፁም ስልጣን ደግሞ ፈፅሞ ያበላሻል) እንዲሉ የአቶ መለስ ስልጣን እንዳበላሻቸው ከመናገር አልቆጠብም፡፡ አቶ መለስ ግን ተበላሽተው አልቀሩም ያበላሹት ብዙ ጉዳይም አለ፡፡ ለምሳሌ የሚከተሉት፡-