Pages

Tuesday, May 31, 2011

የአምባገነን መንግስታት ባሕርያት እና የመለስ እውነታዎች

አምባገነን መንግስታት ከአንድ ባሕር ይቀዳሉ፤ በርካታ የሚመሳሰሉባቸው ባሕርያት አሉዋቸው፡፡ በዚህች መዳፍ በምታክል ገጽ እና በእኔ ቁንፅል እውቀት ሁሉንም ዘርዝሮ መጨረስ ይከብዳል፡፡ ለነገሩ የአምባገነን መሪዎችን የጋራ ባሕርያት እነሱ ራሳቸው በቅጡ አያውቁትም፡፡ ነገር ግን በተለይ ጎልተው የሚለዩባቸውን ባሕርያቶች አንድ፣ ሁለት እያልን እስከአምስት መቁጠር እንችላለን፡፡ እነሆ፡-

Monday, May 30, 2011

ከአሜን ወዲህና ከአሜን ወዲያ ማዶ

በአገራችን ሰው ተመርቆ ሲያበቃ ዝም ማለት የለበትም - ‹‹ከአሜን ይቀራል!›› ይባላል፡፡ አሜን በፀጋ መቀበል፣ ይሁንልኝ፣ ይደረግልኝ እንደማለት ነው፡፡ ይሄ የዓለማችን ዕውቅ ደራሲዎች ‹አዎንታዊ አስተሳሰብ› ወይም ‹ተስፈኝነት› (optimism) የሚሉት ዓይነት እሳቤ ነው፡፡ ሰሞኑን ‹ተኣምራዊው ኃይል› በሚል የተተረጎመውን የርሆንዳ ባይርኔን መጽሃፍ እያነበብኩ ነበር፡፡ የአዎንታዊ አስተሳሰብ አቀንቃኝ ነች፡፡ እኔም የአዎንታዊ አስተሳሰብ አቀንቃኝ ነኝ ባይ ነኝ፤ ሰዎች ግን ብዙ ብሶት ሳወራ ስለሚሰሙ ከአሉታዊዎች ተርታ ያሰልፉኛል፡፡ ለዚያ ነው ዛሬ የ‹አሉታዊ አስተሳሰብ› ወይመ ‹ጨለምተኝነት› (pessimism) አቀንቃኝ ሁኜ ልሟገት የተነሳሁት፡፡

Pessimism ስሙ አያምርም፤ ጨለምተኝነት ነው፡፡ ነገር ግን የስሙን ያህል ክፉ ነው ወይ? ዓለማችንንስ ያቀኗት እውን አዎንታዊ አሳቢዎች (optimists) ብቻ ናቸው? የሁላችንም ጥያቄ ነው፡፡ አዎንታዊ አሳቢዎች(optimists) ስለ አሉታዊ አሳቢዎች (pessimists) ያላቸው አመለካከት ራሱ ጨለምተኛ (pessimist) ነው፡፡ የአሉታዊ አሳቢዎች ድርሻ በአዎንታዊ አሳቢዎች እይታ አፈር ድሜውን በልቷል፤ እየበላ ነው፡፡

በአንድ አስቂኝ አባባል እንጀምር፡-

Thursday, May 12, 2011

"ድር ቢያብር" ለአምባገነኖች ምናቸው ነው?


Gene Sharp የአረቡን ዓለም አብዮት አቀጣጥሏል የሚባልለትን From DICTATORSHIP to DEMOCRACY: a Conceptual Framework for Liberation የተሰኘ ጥናት ጸሃፊ ናቸው፡፡ ጥናቱ የአምባገነኖችን ዓይነት ሲዘረዝር ሚሊቴሪ አምባነገን፣ ከአባት ወደልጅ የሚተላለፍ የንግስና ሥርዓት፣ አሃዳዊ የፖለቲካ ፓርቲ የሚመራው እና የውጭ ወራሪዎች ብሎ ይመድባቸዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን በየትውልዱ አራቱንም ዓይነት አምባገነኖች ለመሸከም ተዳርገናል፡፡ ይኸው አሁንም በአሃዳዊ የፖለቲካ ፓርቲ የሚመራው አምባገነናዊ አስተዳደር ላይ እንገኛለን፡፡

የመለስ ዜናዊን እና ፓርቲያቸውን አምባገነንነት የሚጠራጠር ኢትዮጵያዊ ካለ (ምንም እንኳን የአባይን መገደብ የማይደግፍ ‹‹ኢትዮጵያዊነቱን በገዛ ፈቃዱ ሰርዞታል›› እንደተባለው፣ ኢትዮጵያዊነቱ ይሰረዝ ለማለት ባልደፍርም፤) የአምባገነን ትርጉሙን ሊነግረን ይገባል፡፡

መለስ ዜናዊና ፓርቲያቸው ተለሳልሰው ቦታ፣ ቦታቸውን ከያዙ በኋላ የሚነቀንቃቸው ጠፍቷል፡፡ መጀመሪያ ላይ ብዙው ሕዝብ በጨዋታቸው ተሸውዶ ነበር፤ የምርጫ 97 ድራማ እስኪያጋልጣቸው ድረስ፡፡ ከዚያ በኋላ ግን ለወንበራቸው ምን ያህል ቀናኢ እንደሆኑ በግልፅ አስመስክረዋል፡፡ በመሰረቱ እነመለስ በአናሳ ቡድን አመራራቸው ትልቅ ‹ኢምፓየር› መስርተዋል፡፡ ከስልጣናቸው በምርጫ ከወረዱ ከተጠያቂነት የማያስተርፋቸው ነገር አይጠፋም ስለዚህ በምርጫ ይወርዳሉ ብሎ መመኘት ልጅነት ወይም ጅልነት ነው፡፡

Gene Sharp ቀደም ሲል በጠቀስነው ጥናታቸው ሊዩ ጂ የተባለ ቻይናዊ ጸሃፊ በ14ኛው ክፍለዘመን ከጻፈው ታሪክ ውስጥ የሚከተለውን ያስነብቡናል፡፡

Monday, May 9, 2011

የአባይ ግድብ፣ የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ፣ የባሕር በር እና የወር ደሞዝ


አንዳንድ ደፋሮች ‹‹ኢትዮጵያውያን ምቀኞች ናቸው›› ይሉና አንድ ተረት ይተርታሉ፡፡ እግዚአብሄር አንዱን ኢትዮጵያዊ ‹‹የፈለግከውን ጠይቀኝ እና አደርግልሃለሁ፤ ነገር ግን ላንተ የማደርገውን ነገር በእጥፉ ለጎረቤትህ አደርግለታለሁ›› ብሎ ሲለው ፣ ሰውየው በብርሃን ፍጥነት ‹‹እንግዲያውስ አንድ ዓይኔን አጥፋልኝ›› አለው ይባላል፡፡

የአባይ ግድብ እና የኢትዮጵያውያን ስሜታዊ መንዘርዘር - - -
ኢሕአዴግ የአዋሽ ወንዝን ገድቤ 5000 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል አመነጫለሁ ቢል ኖሮ በአባይ ጉዳይ እንደተወዘወዝነው በደስታ የምንፈነድቅ አይመስለኝም፡፡ ለምን? እውን የመንግስት ሚዲያው እንሚለፍፈው ‹‹ቁጭቱ›› ብቻ ነው? ‹‹አይመስለኝም›› እንዲያውም ያቺ እላይ የጠቀስናት ድብቅ የጋራ ባሕሪያችን አፈንግጣ ወጥታ ነው፡፡ አባይን መገደብ ግብፅን ዋጋዋን መስጠት ስለሚመስለን ነው፡፡ ‹‹የታባቷ›› ዓይነት ነገር!!!

የአባይ ግድብ እና የትራንስፎርሜሽኑ ዕቅድ - - -
እኔ የምለው? የትራንስፎርሜሽኑ ዕቅድ አባይን መገደብ ብቻ ነው እንዴ? ምክንያቱም አሁን የምንሰማው መፈክር እኮ ‹‹ቦንድ በመግዛት እና የወር ደሞዛችንን በመለገስ አባይን ገድበን የትራንስፎርሜሽኑን ዕቅድ እናሳካ›› የሚል ነው፡፡ ቀድሞ ነገር የአባይ ግድብ በትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ውስጥ መቼ ተካተተና፡፡ ተጨማሪ ነገር አይደል እንዴ? ሕዝባዊ አመፅ ባለማስነሳታችን - ምርቃት!!!

የአባይ ግድብ እና የወር ደሞዝ - - -
ሰሞኑን አዲስ አድማስ ላይ ካነበብኩት ወገኛ አባባል አንዱ ‹‹አባይ ድሮ ግንድ ይዞ ይዞር ነበር፤ አሁን ደግሞ ደሞዛችንን ይዞ ይዞራል›› ነው፡፡ በኢትዮጵያ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውስጥ እምብዛም ያልተዋጣለት በአብላጫ ድምፅ የመወሰን ጉዳይ ዘንድሮ ለደሞዝም ውሏል፡፡ በየመስራቤቱ አዳራሽ ቀድሞ የተወሰነው የደሞዝ ስጦታ አጀንዳ ይነሳና፣ የይስሙላ ውይይት ከተደረገበት በኋላ በአብላጫ ድምፅ የያንዳንዱ ሰው ደሞዝ ይወሰዳል፡፡ እኔ የምለው ‹‹የራስን ዕድል በራስ መወሰን›› የምትለዋ የሕገ መንግስታችን አወዛጋቢ ሐረግ ለወር ደሞዝ ሲሆን አትሰራም እንዴ?!

የአባይ ግድብ እና የባሕር በር - - -
የኢሕአዴግ መንግስት አባይን በመገደብ ብቻ ደርሶ አርበኛ ለመመስል ከመሞከሩ በፊት መመለስ ያለበት ጥያቄ ያለ አይመስላችሁም፡፡ ለኢትዮጵያ ከአባይ ግድብ እና ከባሕር በር የትኛው ያስፈልጋት ነበር? እውነቱን ለመናገር ከኤርትራ ጋር አብሮ የሸኘውን ወደባችንን በምንም ሊክስልን አይችልም፤ መቶ ብር ቀምቶ አንድ ብር የሰጠ ቸር አይሰኝም!!!

Wednesday, May 4, 2011

የሚከፈላቸውና የማይከፈላቸው ‹አዳሪዎች›


‹አዳሪ› የሚለውን ቃል የተዋስኩት ከአበባው መላኩ ጣፋጭ የግጥም ስብስብ ውስጥ ነው፡፡ ከግጥሞቹ ስንኞች ጥቂት ቆንጥሬ ጀባ ልበላችሁና ወደጽሁፌ ልንደርደር፡፡

‹‹… ሴትነቴን ወደው፣ እኔነቴን ንቀው፣
በፍቅሬ ተማርከው ገላዬ ስር ወድቀው፣
‹እን’ደር› ይሉኛል በስሜት ታውረው፣
እነሱ ቀድመውኝ በወንድነት አድረው፡፡…››

ጽሁፉ ወንደኛና ሴተኛ አዳሪዎችን ይመለከታል፡፡ በዚህ ወግ ውስጥ እስከዘለቅን ድረስ ‹አዳሪ› ማለት በሴሰኝነት የተጠመዱ ወንዶችና ሴቶችን እንጂ ከተቃራኒ ፆታ ጓደኛቸው ጋር ያደሩ እና የሚያድሩ ሰዎችን አይመለከትም፡፡

በመጀመሪያ ፍቅር ስለመስራት

Tuesday, May 3, 2011

ፅድቅና ኩነኔ


ኢትዮጵያ ሃይማኖቶችርስ በርስ ተከባብረው ተሳስበው የሚኖሩባት ሃገር ነች፡፡ የትዮጵያውያንን ማሕበራዊ ጋርዮሽ የሃይማኖት ልዩነታቸው ላወከውም፡፡ በዚህ ስሌት የሚከተለው ምነትም Aክባሪ ንደማያጣ ተስፋደርጋለሁ፡፡ ምነትና በሃይማኖት መካከል የተሰመረ መስመር መኖሩን ርግጠኝነት መናገርልችልም፡፡

ሃይማኖት ያለምነት ምንም ነውና፡፡ ስለዚህ ንድ ሰው ሃይማኖተኛ ለመሆን ምነት/ማመን ያስፈልገዋል ማለት ነው፡፡ ምላኩን ማመን፣ ቅዱሳት መፃሕፍት የሚናገሩትን ማመን፣ ወይም ጣፈንታው ቀድሞ መፃፍ ማመን፡፡