Pages

Friday, September 30, 2011

የአፋልጉኝ ማስታወቂያ ለተቃዋሚዎች


መጀመሪያ ጭብጨባ

አንድነት ፓርቲ በቅርቡ ተቃዋሚዎች/የተቃዋሚ ደጋፊዎች በቂ የመረጃ ምንጭ የላቸውም በማለት በየሣምንቱ ማክሰኞ፣ በ5 ብር ገበያ ላይ የምትውል ‹‹ፍኖተ ነፃነት›› የተሰኘች ጋዜጣ ማሳተም ጀምሯል፡፡ አንዱአለም አራጌ ሲናገር እንደሰማሁት ‹‹በጋዜጣዋ ላይ የኢሕአዴግ ደጋፊና አባላትም ቢሆኑ መጻፍ ይፈቀድላቸዋል፤ አንድነት እንደ ኢሕአዴግ የመናገር ነፃነትን የማፈን ፍላጎት የለውም፡፡››

ከዚህ በተጨማሪም ፓርቲው በየሣምንቱ እሁድ ማለዳ በተጋባዥ ምሁራን ጽሁፍ አቅራቢነትና በተሳታፊዎች መካከል የሚካሔድ የውይይት ፕሮግራም ጀምሮ ነበር፡፡ (የእነ አቶ አንዱአለም በ‹‹አሸባሪነት›› ተጠርጥሮ መታሰር ይህንን ጠቃሚ ልምድ እስከወዲያኛው ያስቀረው ይሆን?)

በሌላ በኩል (የኔ favorite ባይሆንም እንኳን) ኢዴፓ የዓለም ሊበራል ፓርቲዎችን ጉባኤ በ2004ዓ.ም. በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊያካሒድ ጎንበስ ቀና እያለ መሆኑ የሚያስመሰግን ነው፡፡ እንዲህ ሰበብ እየፈለግን የምናቆለጳጵሳቸው ተቃዋሚዎች ግን በደመስማሳው ስንመለከታቸው መንግስት አንድ ውሳኔ ባሳለፈ ቁጥር የፕሮፓጋንዳ መግለጫ ከመስጠት ባሻገር (ያውም ከሰጡ) ባለፈው ምርጫ ካየናቸው በኋላ የት እንደገቡ ጠፍተዋል፡፡

Thursday, September 22, 2011

ሞክሮ መሳሳት እና ከስህተት መማር


እስኪ የዛሬውን ወጋችንን ብዙ በተደመጠ ቀልድ እንጀምረው፡፡ አንዲት ተማሪ ለፈተና ተቀምጣለች፡፡ ጥያቄዎቹን አየቻቸው ‹እውነት› ወይም ‹ሐሰት› ነው መልሳቸው፡፡ ምንም ባለማጥናቷ የቱ እውነት፣ የቱ ሐሰት እንደሆነ አታውቅም፡፡ የመጣላት አማራጭ ሳንቲም ከኪሷ አውጥታ ‹አንበሳ› ሲሆን ‹እውነት›፣ ተቃራኒ ሲሆን ደግሞ ‹ሐሰት› እያለች መመለስ ነው፡፡ በዚህ መንገድ ፈተናዋን ሰርታ ስትጨርስ በጣም ብዙ ጊዜ ተረፋት ስለዚህ የሰራችው ትክክል መሆን አለመሆኑን ለማረጋገጥ ፈለገች፡፡ ግን ደግሞ ማረጋገጫ መንገድ የላትም፤ ስለዚህ በጀመረችው መንገድ እንደገና ሳንቲም እየወረወረች አንበሳን ለእውነት፣ ጀርባውን ለሐሰት እየመደበች መልሷን ታረጋግጥ ጀመር፡፡

በእንዲህ ዓይነቱ ፈተና ውስጥ ሁለት መልስ ብቻ በመኖሩ፥ ያለሳንቲምም ቢሆን ሞክሮ መሳሳት፣ ሞክሮ ለመማር ነው፡፡ (በፈረንጅ አፍ Trial and Error Learning ይባላል፡፡ በአማርኛ ልተረጉመው ፈልጌ ነበር፤ ከበደኝ እንጂ! ‹ሞክሮ በመሳሳት መማር› ብለው ትክክል ነው እንዴ?) ግን ደግሞ በሕይወት ዓለም እልፍ መንገዶች አሉ፤ የትኛው መጨረሻው እንደሚያምር ለማወቅ ወይ በሁሉም መንገዶች ተራ፣ በተራ መሄድ አሊያም [ወደኋላ የምንመካከርበትን ጉዳይ ማድረግ] ያስፈልጋል፡፡ በሁሉም መንገዶች እየሄድን መጨረሻቸውን እንይ እንዳንል ብዙ ችግሮች አሉ፡፡ ከችግሮቹ አንዱ፡- ለሙከራ የጀመርነው መንገድ መጨረሻው ባያምርስ? እሺ፡- መጨረሻው ሰላም ሆኖ መድረሻውን ስላልወደድነው ብቻ መመለስ ብንፈልግ የምንመለሰው እንዴት ነው? ከሁሉም የሚያሳዝነው ግን ሁሉንም መንገዶች ለመሞከሪያ በቂ ጊዜ የለንም፤ ሕይወት አጭር ናት፡፡

ዓላማቸው ግልጽ ባልሆነ የሐሳብ ድሪቶዎች ይህንን ያህል ካደከምኳችሁ ይበቃል፡፡ የዚህን ጽሁፍ ዓላማ ለማብራራት ግን አሁንም አንድ አንቀፅ ያስፈልገኛል፡፡ ከሰው ጋር ተግባብቶ ለመኖር እየሞከሩ፣ መሳሳት፤ እየተሳሳቱ፣ መማር ይቻል ይሆናል፡፡ በሰዎች ዕጣ ፈንታ ለመወሰን ግን እየሞከሩ መሳሳት፣ እየተሳሳቱ መታረም አይቻልም፡፡ ዕጣ ፈንታ መዳረሻ በመሆኑ ማጣፊያ (undo) የለውም፡፡ በሃገራችን፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚወጡ መመሪያዎች እና ውጤታቸው ግራ ቢያጋቡኝ ይህንን መጻፍ ጀመርኩ፡፡

Thursday, September 15, 2011

መንግስት ያልቻለውን እኛ ብንሞክረውስ?


ጎበዝ! ወሩ የአዲስ ዓመት መጀመሪያ ነው፡፡ የኑሮ ውድነቱን ጉዳይ ካምናው የተሻለ የሚያሰኘው ነገር የለም፡፡ እንዲያውም ከሰሞኑ ሮይተርስ የኢትዮጵያ ስታትስተክስ ኤጀንሲን ጠቅሶ ያስነበበን ዜና እንደሚነግረን ከሆነ የገንዘብ ውድቀቱ ከአምናው ነሐሴ ጋር ሲነፃፀር ባለፈው ወር 40.6 በመቶ አሻቅቧል፡፡ ማለትም የዘንድሮ መቶ ብር መግዛት የሚችለው የአምናው 60 ብር መግዛት የሚችለውን ያክል ብቻ ነው፡፡ ገንዘብን ባንክ በማጠራቀም 40በመቶ ማትረፍ አይቻልም፤ በመነገድም ይህን ያህል ትርፍ ማግኘት ይቻል እንደሆነ እጠራጠራለሁ፡፡ ስለዚህ በደሞዝ ጭማሪ መርካት አይቻልም፤ ጊዜው ራስን የማዳን ነው፡፡ መንግስት ያተመውን ገንዘብ በቦንድ ግዢም አለ በሌላ ሰብስቦ ሊጨርሰው ስላልቻለ የኑሮ ውድነቱ በቅርቡ ላያባራ ይችላል፡፡

ስለሆነም ለኑሮ ዘይቤ ለውጥ ጊዜው ዛሬ ነው፡፡ የኑሮ ውድነትን ማሸነፍ የሚቻለው በኑሮ ዘይቤ ነው፡፡ (5/11 ወይም ቁምሳ ምናምን የተሰኙ የኑሮ ዘይቤዎች እዚህ ቦታ የላቸውም፡፡ ለጸሎት ካልሆነ በቀር እየጾምን ሳይሆን ሳንጾም መኖር መጀመር አለብን)

ዐቢይ ለውጥ

Saturday, September 3, 2011

የሁለት እምነቶች ጦርነት… [ወግ አጥባቂዎች እንዲያነቡት የማይመከር - ክፍል ሦስት]

ጦርነቱ እንደቀጠለ ነው፡፡ ጦር ሜዳው ሕሊና፣ ጦረኞቹ አማኞች እና ኢ-አማኒዎች ናቸው፡፡ በኔ ጦማር ኢ-አማኒዎች ምክንያተኞች እንደሆኑ ይታመናል፡፡ ለዚህም ነው፣ ስለ ኢ-አማኒዎች በተናገርኩ ቁጥር ከአማኒዎች ጋር ማወዳደር የሚቀናኝ፡፡ እንግዲህ በክፍል ሁለት ጽሁፌ ለማመልከት እንደታገልኩት አማኒዎች ከኢ-አማኒዎች አንፃር (ወይም አንግል) ሲታዩ ፈሪዎች፣ ጠባቦችና አምላካችን ብለው በሚጠሩት አካል ላይ ጨካኞች መሆናቸውን ገልጬ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ‹‹ሰነፍ በልቡ እግዚአብሔር የለም ይላል›› (መዝ. 14፥1) የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱሰ ጥቅስ ተንተርሼ ሙግቴን እቀጥላለሁ፡፡ ~ ‹ጎበዝ በይፋ ፈጣሪ የለም ይላል› ወደማለቱ ነኝ፡፡

ኢ-አማኒዎች (atheists) ሞራል የሌላቸውና ማስተዋል የተሳናቸው ተደርገው በአማኒዎች ይሳላሉ፡፡ ኢ-አማኒዎች ከአማኒዎች ይልቅ የሞራል (የሕሊና) ጥያቄን ከግምት ውስጥ ማስገባት የሚችሉና ዓለምን ለመቀየር የሚያስችል አስተውሎት ያላቸው ስለመሆናቸው ጥናቶች ሳይቀሩ ያረጋግጣሉ፡፡