Skip to main content

ለመደገፍ መደገፍ፤ ለመቃወም መቃወም

ቲፎዞነት የጋርዮሽ ስርዓትን ይመስለኛል፡፡ ሰዎች በቡድን ሆነው አንድን ነገር ብቻ በፍጹም ልቦና ለመደገፍ የመቁርባቸው ነገር - ካሰቡት ያስቃል፡፡ ሰዉ ሁሉ በየፊናው የሚደግፈው የእግር ኳስ ቡድን፣ የፖለቲካ ቡድን፣ የሃይማኖት ቡድን፣ የፆታ ቡድን ራሱ ሳይቀር ያበጃል፡፡
ማንቸስተር ዩናይትድ (ብልጫ አወዛጋቢ ቢሆንም) በጨዋታ ብልጫ አርሴናልን ቢረታ እንኳን የአርሴናል ደጋፊዎች ‹‹በጨዋታ በልጠናል›› ብለው መሟገታቸው፣ ወይም ደግሞ የቡና ደጋፊዎች ‹‹ጊዮርጊስ ከፍሏል›› ማለታቸውን አያቆሙም፡፡

የኢሕአዴግ ደጋፊዎች ኢሕአዴግ የፈለገውን ያክል የሚያስቀይም አዋጅ ቢያወጣና ርምጃ ቢወስድ ‹‹ትክክል ነው›› ብለው ሽንጣቸውን ገትረው ከመሟገት አይመለሱም፡፡ የተቃዋሚዎቹም ቡድን እንዲያው ነው፡፡ በእያንዳንዷ የገዢው ፓርቲ ርምጃ ላይ የትችት እና ተቃውሞ በትራቸውን ከማሳረፍ አይመለሱም፡፡ (እሺ - አንመለሰም ካላልኩኝ ራሴን ማፅደቄ ነው፡፡) ከቡድኖቹ ቁማር ጀርባ ያለችውን ሃገር ማሰብም ያስፈልጋል::



የሃይማኖተኞች ቡድንም ከዚህ የተለየ አመለካከት የላቸውም፡፡ የእነርሱ እምነት ብቸኛውና ከፈጣሪ የሚያቆራኝ ሁነኛ መንገድ ሲሆን የሌሎቹ ግን የጥፋት መንገድ ነው፡፡ እመኑኝ እናንተ ስላመናችሁት ብቻ ሃይማኖታችሁ ፍፁምና እውነተኛ አይደለም፡፡ እንዲያ ባይሆንማ ኖሮ በየገዛ ሃይማኖታችሁ እና እምነታችሁ የቀኖና ልዩነትና መከፋፈል ባለተፈታተናችሁ - ነበር!

የፆታ ቡድንም አለ፡፡ ‹‹የፆታ ጋርዮሽ›› እያልኩ እጠራዋለሁ፡፡ ሴቷ ለሴቷ፣ ወንዱ ለወንዱ እየተቧደኑ ‹‹ሴቶች እኮ፤ ወንዶች እኮ›› እየተባባሉ መወነጃጀል በሽ፣ በሽ ነው፡፡

እና ምን ይጠበስ?
ጥሩ ጥያቄ ነው፡፡ የጋርዮሽ ስርዓት (ቡድነኝነት) ያልሰለጠነ ሕዝብ መለያ ነው፡፡ በርግጥ ሰዎች በተናጥል የማይችሉትን ችግር ለመቅረፍ (ሥራ ለመሥራት) ይቧደኑ ይሆናል፡፡ ነገር ግን አንድ አሳብ አይሆኑም፡፡

ስለዚህ?
ስለዚህ መደገፍ ወይም መቃወም ያለብን ቡድኑን ሳይሆን የቡድኑን ሐሳብ መሆኑን አንዘንጋ፡፡ እዚህጋ ለመናገር የፈለግኩት ተቀልብሶ ከፓርቲ ሕልውና አስፈላጊነትጋ የሚቃረን ነገር እንዳልተናገርኩ እንድታውቁልኝ እፈልጋለሁ፡፡ ሆኖም ሁልጊዜ በቡድናችን ውስጥ እውነትና ትክክለኛነት ብቻ እንዳለ ማመን ገደል ይሰዳል፡፡ መቧደናችን ካልቀረ በቡድኑ ውስጥ ያለው ችግር ላንዳችን ካልታየ፣ ለሌላችን ሊታየን ይገባል፡፡

ርቀን ሳንጓዝ በቅርቡ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ኦባማ አሜሪካን ከብድር ቀውስ ለማውጣት እና ቀደም ሲልም የጤና ዋስትናን በተመለከተ ያቀረቧቸው ምክረ ሐሳቦች በበርካታ የገዛ ፓርቲያቸው አባላት (ዴሞክራቶች) ተቃውሞ ገጥሞት - ተፈትኗል፡፡ በመጨረሻ ቢያልፍም፡፡

(እነሱ ስለሰለጠኑ፤) እኛና አሜሪካን አወዳደርክ አትበሉኝና በእኛ ፓርላማ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚያቀርቧቸውን ምክረ ሐሳቦች ለመቃወም የሚዘረጉ የኢሕአዴግ አባላት እጆችን አይተን እናውቃለን? ይሄ የጋርዮሽ (የቡድነኝነት) አስተሳሰብ ነው፡፡ ለመደገፍ ሲሉ ብቻ መደገፍ፡፡

በመጨረሻም
ኢትዮጵያዊ ሆይ፤ የምትደግፈው አካል ሐሳብ ሁሉ እውነት/ጠቃሚ አይደለም፡፡ የምትቃወመው አካል ሐሰብ በሙሉ ሐሰት/ጎጂ አይደለም፡፡ እውነቱ ሁሌም ተቃራኒ ሐሳብ የመኖሩ ጉዳይ ብቻ ነው፡፡

Comments

Popular posts from this blog

The "Corridor Development" is a Façade of the Prosperity Party

Befekadu Hailu I have seen a news report claiming that 40% of central Addis Ababa will be demolished for the corridor development; I am not able to confirm the validity of the news but it sounds real to me given the size of massive operations in the demolition of old neighborhoods and construction of bike lanes, green areas, and glittering street lights. I like to see some beauty added to my city but cannot help mourning the slow death of it too. Addis Ababa was already in a huge crisis of housing and the demolition of houses is exacerbating it. Apparently, Prime Minister Abiy Ahmed is eager to showcase his vision of prosperity by demonstrating how fast his administration can do magic by beautifying the front sides of the streets with lights, new pavements, and painted fences ("to fake it until he makes it" in my friend's words). Therefore, he and his party do not care about the miserable human stories behind the scenes and they will harass you if you tell it (Azeb Woku...

የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ

በፍቃዱ ዘ . ኃይሉ “የአዲስ አበባ ብሔርተኝነት” ቢኖር ኖሮ መሪው ልጅ ሚካኤል ይሆን ነበር። አሁን አሁን እሱ ስለ አዲስ አበባ የዘፈናቸውን ዘፈኖች ቁጥር ራሱ በትክክል መቁጠር ይቸግረኛል። ለአዲስ አበባ ከተዘፈኑ ዘፈኖቹ ውጪም በየዘፈኑ ውስጥ የሚጨማምራቸው መልዕክቶች በራሳቸው መወድሰ አዲስ አበባ ናቸው። ለምሳሌ፣ በቅርቡ በለቀቀው ‘አዲስ አራዳ’ በተሰኘው አልበሙ ውስጥ ‘የድሬ ልጅ’ የሚል ዘፈን አለው። ዘፈኑ የተዘጋጀው ያው የአዲስ አበባ እህት ተደርጋ የምትቆጠረውን ድሬ ዳዋን ለማወደስ ነበር። ልጅ ሚካኤል ግን የአዲስ አበባ ፍቅሩ ያመልጠውና የሚከተለውን ያቀነቅናል፦ “መጣልሽ በሏት፣ ድሬ ድረስ፣  ከአዱ ገነት፣ ከሸገር፣ ከአዲስ ደረሰ፣... የሸገር ልጅ አራዳ ነው፣ ሰው አክባሪ፣ ሰው ወዳዱ፣ ቀላጅና ተረበኛ፣ ፍቅር ይዞ የሚተኛ፣ ‘አለው’ የለ፣ ‘የለው’ የለ፣ ከሁሉ ጋ፣ ግባ ጀባ...፤” ፤ ልጅ ሚካኤል በዚህ አልበሙ ብቻ አዲስ አበባን የሚያውድሰባቸው ሌሎችም ዘፈኖች አሉ፤ ‘ አዲስ አራዳ ’ የሚለው የአልበሙ መጠሪያ እና ‘ሸገር’ የሚሉት ዘፈኖቹ ዋነኞቹ ናቸው። ታዲያ እንዲህ በአዲስ አበባ ፍቅር የሚቃጠለው ልጅ ሚካኤል "ሊነግረን የሚፈልገው ምንድን ነው?" የሚለው ጥያቄ ደጋግሞ ይመጣብኛል። ይህ የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ ምንነትን ለመረዳት የሚጥር ፖለቲካዊ መጣጥፍ ነው። ‘አዲሱ አራዳ’ ማነው? በዚህ ዘፈኑ በብዙዎቻችን ዕድሜ የትዝታ ማኅደር ውስጥ የሚገኙ ነገር ግን በአዲስ አበባ ልማት ሥም የፈረሱ እና እየተረሱ ያሉ ሰፈሮችን ሥም ያነሳሳል። ዘፈኑ በግጥሙም በዜማውም፣ የሐዘን እንጉርጉሮ ያለበት ነው። ምሳሌ እንውሰድ፦ “ጨርሰሽ ስትወጪ ከቡፌ ዳ’ላጋ፣ ጠብቂኝ እንዳልል፣ ቆመሽ መሐሙድ’ጋ፣ አገር ...

መጽሐፍ የሚወጣው፣ የተዋነይ ዘ ጎንጅ 5 መሥመር ቅኔ

ጎንጅ ቅኔ ያጠናበት ደብር ሥም ነው። ደብረ ጥበብ ጎንጅ ቅዱስ ቴዎድሮስ ገዳም። ተዋነይ የባለቅኔው ሥም ነው። (የግዕዝ ትርጉሙ "ዋናተኛ" ማለት ነው።) ሊቁ ተዋነይ የልኅቀቱን ያክል እምብዛም አይወራለትም፤ ነገር ግን በዘመኑ ወደር የሌለው ልኂቅ ስለመሆኑ ሥራው ይናገራል። የሕይወት ተፈራ "Mine to Win" የተሰኘ ድርሰት መቼቱን በዐፄ ዮሓንስ ንግሥና ዘመን፣ በጎጃም/ጎንደር የቅኔ መማሪያ ደብሮች ያደረገ ልብወለድ ነው። ልቦለዱ የቅኔ ትምህርት ስርዓትን ያስተዋውቀናል፤ በበኩሌ የቅኔ ትምህርትን እና የቅኔ ሊቃውንት ታላቅነት ቀድሞ ከነበረኝ ግንዛቤ የበለጠ እንዲሆን አድርጎኛል። በተለይ የተዋነይ ዘ ጎንጅ (በውኑ ዓለም የነበረ ባለቅኔ) ተከታይዋ አምስት መሥመር ቅኔ መጽሐፍ የሚወጣት እንደሆነች ልቦለዱ አሳሰበኝ። ወይም በአጭሩ ብዙ ምዕራባውያን ስንት መጽሐፍ የጻፉለት ፍልስፍናን በአምስት መሥመር ይዟል። የቅኔው ትርጓሜ የመጽሐፍ ቅዱስን እና የመጽሐፍ ቅዱሱን ፈጣሪ ኅልውና ይሞግታል። “የአምን ወይገኒ ኵሉ ዓለም በዘፈጠረ ለሊሁ ብዙኃን እንዘ ይገንዩ ይስግዱ ቅድሜሁ ለነጽሮ ዝኒ ነገር እሥራኤል ከመይፍርሑ ሙሴ ፈጠረ ፈጣሪሁ ወ ፈጣሪ ፈጠረ ኪያሁ።” (ተዋነይ ዘ ጎንጅ። ምንጭ፣ሕይወት ታደሰ ወደአማርኛ የተረጎመችው የሕይወት ተፈራ መጽሐፍ) ትርጉሙን በኋላ እመለስበታለሁ። ስለተዋነይ መጀመሪያ የሰማሁት የበውቀቱ መጽሐፍ ላይ ነበር። እሱም በጨረፍታ - “የሌሊት ዜማዎች” የሚለው ግጥሙ ውስጥ። በውቀቱ ተዋነይን በግጥሙ ግርጌ ማስታወሻው አስተዋውቆን ያልፋል፣ “ተዋነይ በቅኔ ቤት አፈ ታሪክ ሞትን በግዝት ለሰባት ዓመታት ያቆመ ጀግና ነው"። ከዚያ በኋላ፣ አዲስ አድማስ ላይ የወጣ አንድ ጽሑፍ ተዋነይ የተላከበትን ...