Skip to main content

#HRDay2013፤ ከሰው በታች የሆኑ ሰዎች አሉ ብለው የሚያምኑ ኢትዮጵያውያን አሁንም አሉ

ከጥቂት ሳምንታት በፊት ነው፤ አምስት ኢትዮጵያውያን ሰብሰብ ብለን እራት እየበላን ነበር፡፡ አንደኛው በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት ‹‹ነጻ›› የጋዜጠኞች ማኅበራት የአንዱ ፕሬዚደንት ነው፡፡ በጨዋታችን መሐል የተናገረው ነገር ሁላችንንም አስደነገጠን፡፡ በዚህ ዘመን እንዲህ የሚያምን “ዘመነኛ” ሰው አለ እንዴ!?

ሰውዬው ያወራልን ሌሊት ወደጅብነት ስለሚለወጡ ሰዎች ነው፡፡ በዚህ ጊዜ ሁላችንም አፍረን ስናፈገፍግ ከመሐላችን አንዱ “እንዲህ ዓይነት ነገር እውነት ነው ብለህ ታምናለህ?” ብሎ ጠየቀው፡፡ እሱ ሆዬ በሙሉ መተማመን እኛን እንዳላዋቂ በመቁጠር ሌሊት ወደጅብነት የሚለወጡ ሰዎች እንዳሉ ያስረዳን ጀመር፡፡

ይህንን ትዝታዬን የቀሰቀሰው ትላንት ጋዜጠኛ Masresha Mammo የጻፈው ማስታወሻ ነው፡፡ ርዕሰ ጉዳዩ የተለየ ስለነበር እኔ ግን ለዚህች ጽሑፌ የሚጠቅመኝን ገንጥዬ አጣቅሳለሁ፡፡ ማስረሻ እንዲህ ይላል፤

‹‹…ተወልጄ ያደግኹት ከእንጦጦ ተራራ ስር ቀጨኔ በምትባል ሰፈር ውስጥ ነው፡፡ […] ቀጨኔ ላይ ያለው ማኅበረሰብ ወደአዲስ አበባ የተሰደደው የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ሲል አልነበረም፡፡ ቡዳ ነው የሚል ስም ስለተለጠፈበት ‹ልጆቻችንን በልተው ጨረሷቸው› በሚል ግድያው ስለበዛበት ነበር፡፡ አንድ ቀጥቃጭ አባቱ፣ ወይም ሸማኔ ወንድሙ፣ አሊያም ሸክለኛ እናቱ በዚሁ ሰበብ ሲገደሉበት፤ በምላሹ እሱም ደሙን ተወጥቶ ይሸሻል፡፡ ይሰደዳል፡፡...

‹‹ይኼ ማኅበረሰብ ለሺሕ ዓመታት ለኢትዮጵያ ሕዝብ የጀርባ አጥንት ኾኖ ቆይቷል፡፡ በቴክኖሎጂ ላልሰለጠነችው ኢትዮጵያ ማረሻ እና ወገል ያቀርባል፣ እንዳይበርዳቸው ልብስ ይሠራላቸዋል፣ ለመመገቢያቸው የሚኾኑትን ሸክላዎች እና የዕደ ጥበብ ውጤቶች ሁሉ ይሰጣቸዋል፡፡ ያለዚህ ማኅበረሰብ ኢትዮጵያን ወደኋላ ዞር ብላችኹ አስቧት፡፡ [ማኅበረሰቡ] በሚኖርባት በየትኛውም የአገሪቱ ክልል ግን ስሙ ቡዳ ነው፡፡

‹‹ቡዳ ማለት ደግሞ፤ ቀን ቀን ጋቢ ለብሶ የሚኖር፣ ማታ ማታ ወደ ጅብነት የሚቀየር ማለት ነው፡፡ ይህ አስተሳሰብ እና አመለካከት የሚመራው በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ውስጥ ነበር፡፡…››

ማስረሻ ‹‹ነበር›› ይበል እንጂ ዛሬም ድረስ ከዚህ ባልተለየ መንገድ የሚያምኑ ‹‹ምሁራን›› ሳይቀሩ አሉ፡፡ ልዩነቱ በዚህ ዘመን በተለይ በከተማ እንዳይገዳደሉ ሕግ ያግዳቸዋል፤ በገጠር ግን አሁንም በግልጽ አለ፤ ከጥቂት ዓመታት በፊት የሄድኩበት የገጠር አካባቢ ውስጥ ካሉ ‹‹ቡዳ›› ወይም ‹‹ባለእጅ›› ከሚባሉ ሰዎች/ቤተሰብ አባላት ጋር እንዳልገናኝ እና ‹‹ዓይናቸው እንዳልገባ›› አብረውኝ ያሉ ሰዎች ሲጠብቁኝ እና ሲያከላክሉኝ ነበር፡፡ ዛሬም እናቴን ብቻ ሳይሆን ወጣት ጓደኞቼን ሳይቀር ቡዳ የሚባል ነገር የለም ብዬ ማሳመን ይከብደኛል፡፡

ይህ ሰዎችን የማግለያ ሰበብ ነው፡፡ ሰዎችን ንዑስ-ሰው አድርጎ የመቁጠር አባዜ ነው፡፡ የሰብኣዊ መብት ዋና ፅንሰ ሐሳቡ ደግሞ ሰዎች ሁሉ ዕኩል ናቸው የሚለው ነው፡፡ ያንን የማያምኑ ሰዎች ባሉበት አገር በመንግሥት ጥረት ብቻ ሰብኣዊ መብት አይከበርም፡፡
--- 
እዚህ ጽሑፍ ላይ የተሰጡ ለማየት እዚህ ጠቅ ያድርጉ!

Comments

Popular posts from this blog

The "Corridor Development" is a Façade of the Prosperity Party

Befekadu Hailu I have seen a news report claiming that 40% of central Addis Ababa will be demolished for the corridor development; I am not able to confirm the validity of the news but it sounds real to me given the size of massive operations in the demolition of old neighborhoods and construction of bike lanes, green areas, and glittering street lights. I like to see some beauty added to my city but cannot help mourning the slow death of it too. Addis Ababa was already in a huge crisis of housing and the demolition of houses is exacerbating it. Apparently, Prime Minister Abiy Ahmed is eager to showcase his vision of prosperity by demonstrating how fast his administration can do magic by beautifying the front sides of the streets with lights, new pavements, and painted fences ("to fake it until he makes it" in my friend's words). Therefore, he and his party do not care about the miserable human stories behind the scenes and they will harass you if you tell it (Azeb Woku...

የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ

በፍቃዱ ዘ . ኃይሉ “የአዲስ አበባ ብሔርተኝነት” ቢኖር ኖሮ መሪው ልጅ ሚካኤል ይሆን ነበር። አሁን አሁን እሱ ስለ አዲስ አበባ የዘፈናቸውን ዘፈኖች ቁጥር ራሱ በትክክል መቁጠር ይቸግረኛል። ለአዲስ አበባ ከተዘፈኑ ዘፈኖቹ ውጪም በየዘፈኑ ውስጥ የሚጨማምራቸው መልዕክቶች በራሳቸው መወድሰ አዲስ አበባ ናቸው። ለምሳሌ፣ በቅርቡ በለቀቀው ‘አዲስ አራዳ’ በተሰኘው አልበሙ ውስጥ ‘የድሬ ልጅ’ የሚል ዘፈን አለው። ዘፈኑ የተዘጋጀው ያው የአዲስ አበባ እህት ተደርጋ የምትቆጠረውን ድሬ ዳዋን ለማወደስ ነበር። ልጅ ሚካኤል ግን የአዲስ አበባ ፍቅሩ ያመልጠውና የሚከተለውን ያቀነቅናል፦ “መጣልሽ በሏት፣ ድሬ ድረስ፣  ከአዱ ገነት፣ ከሸገር፣ ከአዲስ ደረሰ፣... የሸገር ልጅ አራዳ ነው፣ ሰው አክባሪ፣ ሰው ወዳዱ፣ ቀላጅና ተረበኛ፣ ፍቅር ይዞ የሚተኛ፣ ‘አለው’ የለ፣ ‘የለው’ የለ፣ ከሁሉ ጋ፣ ግባ ጀባ...፤” ፤ ልጅ ሚካኤል በዚህ አልበሙ ብቻ አዲስ አበባን የሚያውድሰባቸው ሌሎችም ዘፈኖች አሉ፤ ‘ አዲስ አራዳ ’ የሚለው የአልበሙ መጠሪያ እና ‘ሸገር’ የሚሉት ዘፈኖቹ ዋነኞቹ ናቸው። ታዲያ እንዲህ በአዲስ አበባ ፍቅር የሚቃጠለው ልጅ ሚካኤል "ሊነግረን የሚፈልገው ምንድን ነው?" የሚለው ጥያቄ ደጋግሞ ይመጣብኛል። ይህ የልጅ ሚካኤል አዲስ አበባ ምንነትን ለመረዳት የሚጥር ፖለቲካዊ መጣጥፍ ነው። ‘አዲሱ አራዳ’ ማነው? በዚህ ዘፈኑ በብዙዎቻችን ዕድሜ የትዝታ ማኅደር ውስጥ የሚገኙ ነገር ግን በአዲስ አበባ ልማት ሥም የፈረሱ እና እየተረሱ ያሉ ሰፈሮችን ሥም ያነሳሳል። ዘፈኑ በግጥሙም በዜማውም፣ የሐዘን እንጉርጉሮ ያለበት ነው። ምሳሌ እንውሰድ፦ “ጨርሰሽ ስትወጪ ከቡፌ ዳ’ላጋ፣ ጠብቂኝ እንዳልል፣ ቆመሽ መሐሙድ’ጋ፣ አገር ...

መጽሐፍ የሚወጣው፣ የተዋነይ ዘ ጎንጅ 5 መሥመር ቅኔ

ጎንጅ ቅኔ ያጠናበት ደብር ሥም ነው። ደብረ ጥበብ ጎንጅ ቅዱስ ቴዎድሮስ ገዳም። ተዋነይ የባለቅኔው ሥም ነው። (የግዕዝ ትርጉሙ "ዋናተኛ" ማለት ነው።) ሊቁ ተዋነይ የልኅቀቱን ያክል እምብዛም አይወራለትም፤ ነገር ግን በዘመኑ ወደር የሌለው ልኂቅ ስለመሆኑ ሥራው ይናገራል። የሕይወት ተፈራ "Mine to Win" የተሰኘ ድርሰት መቼቱን በዐፄ ዮሓንስ ንግሥና ዘመን፣ በጎጃም/ጎንደር የቅኔ መማሪያ ደብሮች ያደረገ ልብወለድ ነው። ልቦለዱ የቅኔ ትምህርት ስርዓትን ያስተዋውቀናል፤ በበኩሌ የቅኔ ትምህርትን እና የቅኔ ሊቃውንት ታላቅነት ቀድሞ ከነበረኝ ግንዛቤ የበለጠ እንዲሆን አድርጎኛል። በተለይ የተዋነይ ዘ ጎንጅ (በውኑ ዓለም የነበረ ባለቅኔ) ተከታይዋ አምስት መሥመር ቅኔ መጽሐፍ የሚወጣት እንደሆነች ልቦለዱ አሳሰበኝ። ወይም በአጭሩ ብዙ ምዕራባውያን ስንት መጽሐፍ የጻፉለት ፍልስፍናን በአምስት መሥመር ይዟል። የቅኔው ትርጓሜ የመጽሐፍ ቅዱስን እና የመጽሐፍ ቅዱሱን ፈጣሪ ኅልውና ይሞግታል። “የአምን ወይገኒ ኵሉ ዓለም በዘፈጠረ ለሊሁ ብዙኃን እንዘ ይገንዩ ይስግዱ ቅድሜሁ ለነጽሮ ዝኒ ነገር እሥራኤል ከመይፍርሑ ሙሴ ፈጠረ ፈጣሪሁ ወ ፈጣሪ ፈጠረ ኪያሁ።” (ተዋነይ ዘ ጎንጅ። ምንጭ፣ሕይወት ታደሰ ወደአማርኛ የተረጎመችው የሕይወት ተፈራ መጽሐፍ) ትርጉሙን በኋላ እመለስበታለሁ። ስለተዋነይ መጀመሪያ የሰማሁት የበውቀቱ መጽሐፍ ላይ ነበር። እሱም በጨረፍታ - “የሌሊት ዜማዎች” የሚለው ግጥሙ ውስጥ። በውቀቱ ተዋነይን በግጥሙ ግርጌ ማስታወሻው አስተዋውቆን ያልፋል፣ “ተዋነይ በቅኔ ቤት አፈ ታሪክ ሞትን በግዝት ለሰባት ዓመታት ያቆመ ጀግና ነው"። ከዚያ በኋላ፣ አዲስ አድማስ ላይ የወጣ አንድ ጽሑፍ ተዋነይ የተላከበትን ...