ጦርነቱ እንደቀጠለ ነው፡፡ ጦር ሜዳው ሕሊና፣ ጦረኞቹ አማኞች እና ኢ-አማኒዎች ናቸው፡፡ በኔ ጦማር ኢ-አማኒዎች ምክንያተኞች እንደሆኑ ይታመናል፡፡ ለዚህም ነው፣ ስለ ኢ-አማኒዎች በተናገርኩ ቁጥር ከአማኒዎች ጋር ማወዳደር የሚቀናኝ፡፡ እንግዲህ በክፍል ሁለት ጽሁፌ ለማመልከት እንደታገልኩት አማኒዎች ከኢ-አማኒዎች አንፃር (ወይም አንግል) ሲታዩ ፈሪዎች፣ ጠባቦችና አምላካችን ብለው በሚጠሩት አካል ላይ ጨካኞች መሆናቸውን ገልጬ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ‹‹ሰነፍ በልቡ እግዚአብሔር የለም ይላል›› (መዝ. 14፥1) የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱሰ ጥቅስ ተንተርሼ ሙግቴን እቀጥላለሁ፡፡ ~ ‹ጎበዝ በይፋ ፈጣሪ የለም ይላል› ወደማለቱ ነኝ፡፡
ኢ-አማኒዎች (atheists) ሞራል የሌላቸውና ማስተዋል የተሳናቸው ተደርገው በአማኒዎች ይሳላሉ፡፡ ኢ-አማኒዎች ከአማኒዎች ይልቅ የሞራል (የሕሊና) ጥያቄን ከግምት ውስጥ ማስገባት የሚችሉና ዓለምን ለመቀየር የሚያስችል አስተውሎት ያላቸው ስለመሆናቸው ጥናቶች ሳይቀሩ ያረጋግጣሉ፡፡
ኢ-አማኒዎች (atheists) ሞራል የሌላቸውና ማስተዋል የተሳናቸው ተደርገው በአማኒዎች ይሳላሉ፡፡ ኢ-አማኒዎች ከአማኒዎች ይልቅ የሞራል (የሕሊና) ጥያቄን ከግምት ውስጥ ማስገባት የሚችሉና ዓለምን ለመቀየር የሚያስችል አስተውሎት ያላቸው ስለመሆናቸው ጥናቶች ሳይቀሩ ያረጋግጣሉ፡፡