Monday, September 30, 2013

Ethiopia’s UDJ Public Demonstration Got Its Route Blocked By Police; Protest Held Anyway!



ON SEPTEMBER 29, 2013 major opposition party of Ethiopia, UDJ (Unity for Democracy and Justice), in collaboration with the coalition of 33 political parties held a brief public demonstration in protest against the controversial Anti-Terrorism Proclamation No. 652/2009 and other human and democratic rights violations. The demonstration was called as a closure to the party’s three months long campaign titled “Millions of Voices for Freedom”.

The demonstration got its route blocked by police in the very beginning however thousands of demonstrators could chant their oppositions in the spot where it was started. Many applauded these demonstrators for they took risk to face the infamous brutality of police in Ethiopia and kept themselves peaceful until the dispersion of the gathering.  

Police blocked the demonstration route to Mesqel square reasoning out that Mesqel square is under construction of the city railroad. This, however, didn’t satisfy the organizers of the demonstration because the square hosted a demonstration called by Union of Religious Institution and Ministry of Federal Affairs a month ago as well as another religious event called Mesqel where hundreds of thousands people attended just three days before this demonstration was called.

The government officials instead suggested the demonstration to be held in a compound known as ‘Janmeda’ which is a few kilometers away from the head office of UDJ. The organizers refused to accept that proposal mentioning the fact that the compound is 100 meters away from a military camp and that according to Demonstration Proclamation No. 003/1991 Article 7/2 – which enforces demonstrations to be held at least 500 meters away from any military camp.

Tuesday, September 24, 2013

የ‘ያ ትውልድ’ መጽሐፍ ማሳተም ለ‘ይህ ትውልድ’ ምኑ ነው?

ከክፍሉ ታደሰ መጽሐፍ በመዋስ በተለምዶ ‘ያ ትውልድ’ እያልን የምንጠራው ትውልድ በ1966ቱ አብዮት ወቅት ወጣት የነበረውን ትውልድ ነው። አሁን በቅርቡ ከተጻፉት ውስጥ፣ (1) ዻንዲ — የነጋሶ መንገድ፤ (2) ሕይወት ተፈራ —   ‘Tower in The Sky’፤ (3) ዶ/ር መረራ ጉዺና — ‘የኢትዮጵያ ፖለቲካ ምስቅልቅል ጉዞና የሕይወቴ ትዝታዎች’፤ (4) ኢ/ር ኃይሉ ሻወል — ‘ሕይወቴና የፖለቲካ እርምጀዬ’ (?)፤ (5) ቡልቻ ዸመቅሳ—  My Life and My Vision ይገኙበታል። እዚህ ውስጥ ያልጠቃቀስኳቸውም ሌሎችም ብዙ አሉ። ሆኖም ማውራት ለምፈልገው የጠቀስኳቸው ይበቁኛል።

ከጠቀስኳቸው የ‘ያ ትውልድ’ ጸሐፍት ውስጥ የአሁኑ ፖለቲካ ውስጥ የሌለችው ሕይወት ተፈራ ብቻ ነች። ሆኖም ሁሉም የሚጋሩት አንድ ነገር ያለ ይመስለኛል፤ የ‘ያ ትውልድ’ ፀሐይ እየጠለቀች መሆኑን በማመናቸው። ይህን ማመናቸውን በግምት ነው የምናገረው። ነገር ግን እነዚህ ሁሉ የሕይወት ልምድን ማጋራቶች አንድም ከእርምጃዎቻቸውና ስህተቶቻቸው እንድንማር፣ አሊያም ደግሞ ሕልሞቻቸውን ከግብ እንድናደርስ ነው። የተጻፉት መጽሐፍት በቂ ባይሆኑም ‘ይህ ትውልድ’ ግን ያለበቂ ትምህርትም ቢሆን አገሪቱ እጁ ላይ መውደቋ አይቀርም። ትውልዱ ይህን አውቆ ተዘጋጅቷል?

“እናቸንፋለን” ወይስ “እናሸንፋለን”?

መጽሐፍ እየጻፈ ያለው ‘ያ ትውልድ’ ብቻ ሳይሆን ‘ይህ ትውልድ’ም ጭምር ነው። (ይህ ትውልድ የምለው ከሀያዎቹ አጋማሽ እስከአርባዎቹ አጋማሽ ያለውን ነው።) ለምሳሌ የልደቱ አያሌው ‘ሦስተኛው አማራጭ’፣ የግርማ ሰይፉ ‘የነፃነት ዋጋው ስንት ነው?’፣ የአንዱዓለም አራጌ ‘ያልተኬደበት መንገድ’ እና ሌሎችም እየወጡ ነው። የነዚህኞቹ ከነዛኞቹ የሚለየው አማራጭ መንገዶች ማመላከት ላይ ወይም ያልተኬደበትን መንገድ ማፈላለግ/ማመላከት ላይ ያተኩራል። የተሄደበትን ከያኛው፣ ያልተሄደበትን በይህኛው ማለት ነው።

‘ይህ ትውልድ’ ከ‘ያ ትውልድ’ ስህተት መውሰድ የሚገባው የመጀመሪያው ትምህርት በጥቂት ልዩነት ጎራ ለይቶ አለመቀጣቀጥን ነው ባይ ነኝ። ‘ያ ትውልድ’ በአንድ ርዕዮተ ዓለም፣ በአንድ ዓይነት ሕልም በቃላት አጠቃቀም ውስጥ ለውስጥ በአንጃነትና በሌላም በሌላም ሲከፋፈልና ሲቆራቆዝ እዚህ ደርሷል —  ቢያንስ እስከ ምርጫ 97። ልዩነትን አቻችሎና ተወያይቶ የመፍታት፣ ከነልዩነትም ቢሆን  (ከ“እናቸንፋለን”፣ “እናሸንፋለን” ዓይነት ትናንሽ የቃላትና አተረጓጎም ልዩነት ይልቅ) በዋነኛ አገራዊ ጉዳዮች (ዴሞክራሲ ማምጣት፣ ድህነትን ማጥፋት… የመሳሰሉት) ላይ ማተኮር ያስፈልጋል።
“እኔ ያልኩት ካልሆነ” የሚለው የቃል ሐረግ ካልሞተ የ‘ያ ትውልድ’ ፀሐይ ብትጠልቅም የ‘ይህ ትውልድ’ ፀሐይ አትወጣም።

እናሸንፋለንም፣ እናቸንፋለንም

አንተ ወይም እኔ (እኔ ወይም ሞት) ሞቷል። አሁን ያለው አማራጭ እኔንም አንተንም አካታች የሆነ አማራጭ ብቻ ነው፤ አንዱ ሲያሸንፍ/ሲያቸንፍ ሌላው የማያጎድልበት፣ ሁሉም የሚያሸንፍበት/የሚያቸንፍበት ነው።

ይሄ ትውልድ በኔ እምነት ከያ ትውልድ ይሻላል። በቀኖና የሚነገሩት የ‘ያ ትውልድ’ ድርሳናት ‘ይህን ትውልድ’ የሚያጣጥሉት በያ ትውልድ መለኪያ እየመዘኑት ነው። ይህ ትውልድ የራሱ መንገድ አለው ብዬ አምናለሁ።  ስለአንባቢነት የሚወራውም ቢሆን ተጨባጩን እውነታ ያላገናዘበ ብዥታ ነው ብዬ የምረዳው። ብዙኃኑ ያኔም ሆነ አሁን ኖሮ አላፊ ነው። ልሒቁ ነው ለውጥ የሚያመጣው። ማንም ማንንም የማያጠፋበት የለውጥ መንገድ ደግሞ በዚህ ትውልድ እጅ አለ ብዬ አምናለሁ።
መልካም የለውጥ መንገድ!

Monday, September 16, 2013

#Ethiopia has a prison-in-a-prison for its journalists



Ethiopian government is the only government of our planet that has prosecuted 12 journalists in relation to ‘terrorism’ and yet says ‘there is no journalist jailed for what it has written’. A teacher and Journalist Reeyot Alemu, is one of these convicted journalists in “supporting terrorism”. She was accused for taking pictures of graffiti (the word ‘beqa’ (enough) written in a street wall - that is said by the government ‘were written to incite terrorism’) and sending them to Ethiopian Review, a website where she worked as a reporter and owned by an Ethiopian diaspora, Elias Kifle (who himself is convicted in absentia).

I had gone to Kality to visit Reeyot Alemu on August 26, 2013 and I joined her sister, Eskedar Alemu, right at the door of Kality prison. One of the door guards told us that only relatives are allowed to visit Reeyot. We argued a little and she let us pass. We have explained the incident to Reeyot. She then told us that she was also under pressure from the prison officials enforcing her to list names of her visitors. Her eyes were shading tears when she said:

“No, I can’t. I can’t because my visitors are not only family and relatives. I have many friends who visit me every time and it is my constitutional right to be visited by every one of them. I told them I won’t be visited by anyone if everyone is not allowed to…”

15 days later, on the eve of Ethiopian New year – Sep. 10, 2013, the news that Reeyot Alemu went on hunger strike came out. Her strike was a reaction to the restrictions of visitors. “She was told that either of her father, mother or her ‘God father’ would be the only people who are allowed to visit her”, says Eskedar; even her fiancé, Sileshi Hagos, and other family members are not allowed to.

The same had happened to journalist Eskinder Nega. For more than two years, he was given only a ‘piece’ of his right to be visited by his wife and child but no one else. Now, he once again is granted back his rights of being visited by anyone since a few months ago. However, there is no reason uncovered about either the prior restriction or recent permission of visitors to him.

Tuesday, September 10, 2013

2005 ቢደገም አልጠላም!


ዓመት በመጣ ቁጥር የግል ስኬቴን የምመዘግብበትና ዓመቱ ሲያልቅ የምለካበት አጭር ጽሑፍ አዘጋጃለሁ፡፡ ብዙ ጊዜ ከመቶ 40 እንኳን አይሳካልኝም፡፡ በሌላ ጽሑፍ በተረክኩት የመታሰር ገጠመኜ (…የቀይ ለባሾቹ ውሎና አዳር…) ፖሊሶች ወስደው ካስቀሩብኝ ብጭቅጫቂ ወረቀቶች መካከል የ2005 ዕቅዴ ይገኝበታል፡፡ በዚህ መሠረት ዓመቱ ቢደገም የማልጠላው አንድም የተሳካ ስለመሰለኝ፣ አሊያም አለመሳካቱን መለኪያ ስለሌለኝ ይሆናል ማለት ነው፡፡

2005 ብዙ የማኅበራዊ አውታር ወዳጆቼ እንደተስማሙበት አስተማሪ ነበር፡፡ እንዲያውም አንድ ወዳጄ እንዳለው ‹‹የዘንድሮው ማንነትህ፣ የአምናውን ቢያገኘው ተበሳጭቶበት በጥፊ ይመታዋል፡፡›› ማኅበራዊ አውታሮች (በተለይም ፌስቡክ) በኢትዮጵያ ወቅታዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ የሞቀ ሙግት በማስነሳት የአስተሳሰብ እና የውይይት ልምዳችንን ይሞግቱታል፡፡ ፌስቡክ ሰዎች በሙሉ ዕኩል ቢሆኑ ሊፈጠር የሚችለውን ነገር ማሳያ መሣሪያ እየሆነ ነው፡፡ ስንቶች በጥንቃቄና በስንት ልፋት የገነቡት በአንዲት ቃል የሚፈርስበት፣ ስንቶች ሊያፈርሱት የደከሙለት በሌላ አንድ ቃል የሚገነባበት መድረክ ነው፡፡ የሕዝባችን ጥንካሬም ድክመትም የሚስተዋልበት ገጽ ነው፡፡ ፌስቡክ ብስጭታችንን ማደቢያ (anger management) ትምህርት ቤት ነው፡፡ እውነቱም፣ ሐሰቱም ገዝፎ የሚታይበት ዓለም ነው፡፡ ፌስቡክ ከነድክመቱም ቢሆን መደበኛውን መገናኛ ብዙኃን (mainstream media) አጀንዳ እየሰጠ ይመግበው ጀምሯል፡፡

Tuesday, August 6, 2013

Things #Ethiopia Do To Sabotage Freedom of Expression

The May 2005 election is a turning point for Ethiopian political sphere, so is for the Freedom of Expression in the country. The election ended with electoral board’s announcement that the incumbent is a winner of the election which oppositions called rigged. Major opposition of the time, CUD, supporters went out in the streets to protest which had ended in death of nearly 200 people when the government tried to crackdown.

EPRDF, the ruling coalition, said it took lessons from the election in its news outlet ‘Abiyotawi Democracy’. In the first term of five years since the election, many changes of control were effected against the people. Apparently, Freedom of Expression is the first of the most victims. Here are a few of the systematic approaches the government used to ban the freedom.

Rule By Law

Controversial proclamations for violating constitutional rights were passed during the first term of post 2005 election. Among these are included the amendment of the Press Proclamation, the Anti-Terrorism Proclamation and the Civil-Societies Proclamation. The latter one entirely banned the role of civil societies in ‘rights’-related activities where as the former two contained articles that limited freedom of expression given in article 29 of the Ethiopian constitution.

Since these proclamations were passed, at least eight journalists are convicted in relation to terrorism and if you ask any ordinary citizen whether or not these journalists are terrorists, the most probable answer is definitely ‘No!’.

Monday, May 27, 2013

#Ethiopia: ከቃሊቲ ወደ ዝዋይ፤ ለምን?


ልክ የዛሬ 22 ዓመት (ማክሰኞ ዕለት)፣ በግንቦት 20 ኢሕአዴግ ቤተ መንግሥቱን ተቆጣጠረ፡፡ በዕለቱ በኢትዮጵያ ሬድዮ እየተደጋገመ ይተላለፍ የነበረው ‹‹ደርግ ሲጠቀምበት የነበረውን… ለሰፊው ሕዝብ ጥቅም ሲባል… ተቆጣጥሮታል›› የሚሉት ቃላት ያሉበት እወጃ ነበር፡፡ ከ22 ዓመት በኋላ ‹ደርግ ሲጠቀምበት የነበረው፣ ኢሕአዴግ እየተጠቀመበት ነው› ማለት ብቻ ይቻላል፡፡ የ‹‹ሰፊው ሕዝብ›› ጥቅምና ተሳትፎ ተመናምኖ፣ ተመናምኖ አሁን የደረሰበትን ትክክለኛ ቦታ መገመት ያስቸግራል፡፡ ስለሆነም የኢሕአዴግ መንግሥት ‹‹እየተጠቀመበት›› ያለውን ነገር እያስጠበቀ ያለው በአፈና ነው፡፡ በምርጫ አፈና፣ በሚዲያ አፈና፣ በፖለቲከኞች አፈና… ወዘተ፡፡

የዛሬ አራት ዓመት ገደማ በሚያዚያ ወር አጋማሽ ላይ በመንግሥት ባለሥልጣናት ‹‹የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ›› ተብሎ የነበረውና በኋላ ደግሞ በፍርድ ቤት ‹‹ሕገ መንግሥቱን በኃይል የመናድ ሙከራ›› ተብሎ በቀረበው ክስ 23 ሰዎች በቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ አንዱ የሞት ፍርድ እና ቀሪዎቹ ደግሞ የዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት ተበይኖባቸዋል፡፡

ስለነዚህ እስረኞች መዘንጋት እና የቤተሰቦቻቸው ሁኔታ ከአንድ ወር በፊት ዞን ዘጠኝ ላይ የወ/ሮ እማዋይሽን ልጅ በማነጋገር የተጻፈውን ማንበባችን ይታወሳል፡፡ አሁን ደግሞ ከነዚህ እስረኞች መካከል በእነብ/ጄኔራል ተፈራ ማሞ መዝገብ ከተከሰሱት 23 ‹‹ታራሚዎች›› መካከል ከ4ቱ በስተቀር (19ኙ) ወደዝዋይ በቅርቡ ተዛውረዋል፡፡ ዝውውሩ እነርሱን ብቻ የተመለከተ ባይሆንም፣ ድንገተኛነቱ እና ምክንያት ያልተሰጠበት መሆኑ ጥያቄዎችን እንድናነሳ ያስገድደናል፡፡

ወደዝዋይ ከተዘዋወሩት መካከል ቃሊቲ እንዲቀሩ የተደረጉት አቶ መላኩ ተፈራ ጥላሁን (የሞት ፍርድ)፣ ወ/ሮ እማዋይሽ ዓለሙ (ዕድሜ ልክ)፣ ሌትናንት ኮ/ጌታቸው ብርሌ (ዕድሜ ልክ) እና ኮነሬል ፋንታሁን ሙሃባ (ዕድሜ ልክ) ናቸው፡፡ እነዚህ እስረኞች ከሌሎቹ ተለይተው ለምን እንደቀሩ (ወይም የተዛወሩት ለምን ተለይተው እንደተዛወሩ) ያነጋገርኳቸው ቤተሰቦች ምንም የሚያውቁት እንደሌለ ዘርዝረው ነግረውኛል፡፡ የቃሊቲው ማረሚያ ቤት የመጣበብ ችግር ገጥሞት ይሁን/አይሁን፣ ሌሎች ታራሚዎች ሊመጡበት ታስቦ ይሁን/አይሁን የሚታወቅ ሌላ መረጃ የለም፡፡

የታራሚዎቹ ወደቃሊቲ መዛወር በተለይም ቀድሞ ነዋሪነታቸው አዲስ አበባ የነበሩ በመሆናቸው እና ቤተሰቦቻቸውም በአዲስ አበባ የሚኖሩ በመሆናቸው ትልቅ ፈተናን በጠያቂዎቻቸው ላይ እና በታራሚዎቹም በራሳቸው ላይ ያሳድራል፡፡ ወትሮም ቃሊቲ ድረስ (በየቀኑ ቀርቶ) በየሳምንቱ እንኳን ለመመላለስ የኢኮኖሚም ይሁን የሌላ አቅም ችግር ላለባቸው ቤተሰቦች የታራሚዎቹ ወደዝዋይ መዘዋወር በረዥም ጊዜ አንዴ ብቻ እንዲጠያየቁ የሚያስገድድ ብያኔ ነው፡፡ ታራሚዎች በሚኖሩበት ክልል የመታሰር መብት አላቸው ወይም የላቸውም የሚለውን ጥያቄ ለሕግ ሰዎች ብንተወው እንኳን መንግሥት እንደሞራል አባትነቱ የታራሚዎቹን እና ቤተሰባቸውን እንግልት ለመቀነስ የሚጠበቅበትን ሞራላዊ ግዴታ እየተወጣ እንዳልሆነ መታዘብ ይቻላል፡፡
ከዚህም በላይ፣ በቅርቡ ወደዝዋይ የተዘዋወረውን ጋዜጠኛ ውብሸት እዚያው ዝዋይ ነዋሪ ሁነው ሊጠይቁት የሄዱ ሰዎችን ‹‹ከዝዋይ መጠየቅ አይቻልም›› በሚል የዝዋዩ ማረሚያ ቤት እንደመለሳቸው ሰምተናል፡፡ ይህም ሌላው ሕገ ወጥ እና ኢሞራላዊ ድርጊት ነው፤ ለታዛቢም ‹ታራሚዎቹ ወደ ዝዋይ የሚዛወሩት በብቸኝነት እንዲቀጡ ነው ወይ?› ብሎ እንዲጠይቅ ያስገድዳል፡፡

የ‹‹ታራሚ››ዎቹ አያያዝ

የታራሚዎች አያያዝ ከእስረኛ እስረኛ የተለያየ እንደሆነ ከተለያዩ ምንጮች መስማት የተለመደ ነው፡፡ ከፖለቲካ ጋር በተነካካ ጉዳይ የታሰሩ ታራሚዎች በ‹‹ሌላ›› ወንጀል ድርጊት ከታሰሩ ሰዎች ያነሰ መብት ያላቸው የሚመስልበት አሠራር አለ፡፡ የቃሊቲው ማረሚያ ቤት እነዚህን የ‹‹ፖለቲካ እስረኞች›› አይደሉም የሚላቸውን የፖለቲካ እስረኞች የመጠ’የቂያ ሰዓታቸውን በልዩነት አስቀምጦታል፡፡ ሌሎቹ ታራሚዎች ቅዳሜና እሁድ ጠዋቱን ሙሉ የሚጠየቁ ቢሆንም፣ የፖለቲካ እስረኞች ግን ከ6፡00 ሰዓት እስከ 6፡30 ለግማሽ ሰዓት ብቻ እንዲጠየቁ ይደረጋሉ፡፡ ታራሚዎቹ ሲጠየቁ ከወዳጅ ቤተሰቦቻቸው ጋር የሚወያዩትን ለማድመጥ እንዲችሉ ጠባቂዎቻቸው ከአጠገባቸው ይቆማሉ፡፡ መጽሐፍቶች ተመርምረው እና ታይተው ብቻ ነው የሚገቡላቸው፡፡ አንዳንዴ ፖለቲካ ያልሆኑ ፖለቲካ የሚመስሉ መጽሐፍቶች ሳይቀሩ እንዳይገቡ ይታገዳሉ፤ ለምሳሌ ‹የሎጥ ሚስት› የሚለው ልቦለድ ለጋዜጠኛ ውብሸት እንዳይገባ ታግዶበታል፡፡

አቶ ስዬ አብርሃ እና አቶ ታምራት ላይኔ በእስር ላይ በነበሩበት ጊዜ በእስር በነበሩባቸው ጊዜ ምግብ አሙቀው ለመብላት የሚያስችላቸው ቁሳቁስ ገብቶላቸው የነበረ መሆኑ ይታወሳል፡፡ በተጨማሪም፣ የማረሚያ ክፍሎቹ የጋራ መፀዳጃ ቤት እና ሻወር ቢኖራቸውም ንፅሕናቸው የተጠበቀ ባለመሆኑ ሁለቱም ታራሚዎች ማታ፣ ማታ ወጣ ብለው እስከ አራት ሰዓት አምሽተው እንዲመለሱ ተፈቅዶላቸው ራታቸውን ሁሉ ሳይቀር ውጪ በልተው ይመለሱ እንደነበር - ስለእስረኞች አያያዝ ለማጣራት ሙከራ ሳደርግ ሰምቻለሁ፡፡

እነዚህ ሁሉ ለነአቶ ስዬ ሲደረጉ የነበሩ እንክብካቤዎች ግን ለሌሎቹ የፖለቲካ እስረኞች የሚሞከሩ አይደሉም፡፡ እንዲያውም የማረሚያ ቤቱን እራት እስከ 10 ሰዓት ድረስ መብላት እና እስከ 12 ሰዓት ድረስ ተፀዳድቶ መግባት በተለይ የቃሊቲ ማረሚያ ቤት (የፖለቲካ እስረኞቹ) አያያዝ ‹‹ደንብ›› ነው፡፡

አቶ መላኩ ተፈራ ‹‹ሕገ መንግሥቱን ለመናድ መሞከር›› በተባለው ክስ የሞት ቅጣት የተበየነባቸው ፍርደኛ ናቸው፡፡ አቶ መላኩ ተፈራ ‹‹የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ መሥራች፣ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የሰሜን ኢትዮጵያ ዋና አደራጅ - የሙሉ ቀን ፖለቲከኛ›› እንደነበሩ ነግረውኛል፡፡ በዕድሜያቸው ገፋ ያሉ እና አልፎ አልፎ ከውጭ አገር እየመጡ ከሚጠይቋቸው ልጆቻቸው በቀር በቋሚነት የሚጠይቋቸው ባለቤታቸው ብቻ ናቸው፡፡ ሁለቱም በዕድሜ ከፍ ያሉ በመሆናቸው ለሳምንታዊዋ 30 ደቂቃም ቢሆን አረፍ ብለው መነጋገር የሚችሉበት ሁኔታ እንዲመቻች ቢጠይቁም ማረሚያ ቤቱ ምላሽ ሳይሰጣቸው ጆሮ ዳባ ልበስ እንዳለ አጫወተውኛል፡፡

እርሳቸው የደም ግፊት እና የነርቭ በሽታ እንዳለባቸው ቢናገሩም፣ በወር አንዴ የደም ግፊቱን መድኃኒት ይዘው ከሚመጡት የጤና ባለሙያዎች ጋር ከመገናኘት በላይ ክትትል አይደረግላቸውም፡፡ በቅርቡ እንደሰማነው ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙም በገጠማት የጤና ችግር አፋጣኝ እና ጥሩ ሕክምና እንድታደርግ መፍቀድ ቀርቶ በረዥም (ያውም ለታካሚዋ ቀኑ በማይነገር) የሕክምና ቀጠሮ በማመላለስ የጤንነቷ ሁኔታን ስጋት ውስጥ ሊገባ የሚችልበትን ዕድል ማረሚያ ቤቱ በቸልተኝነት ፈቅዷል፡፡ በጥቅሉ የማረሚያ ቤቱ አያያዝ በተለይም የፖለቲካ እስረኞች ላይ የሁለትዮሽ (የማግለል) አቋም ያራምዳል ማለት ይቻላል፡፡

በእነብ/ጄኔራል ተፈራ ማሞ መዝገብ የተከሰሱት ታራሚዎች ይቅርታ ከጠየቁ የከረሙ ቢሆንም አሁንም መንግሥት /ማረሚያ ቤቱ/ ሊፈታቸው ፈቃደኛ ሳይሆን፣ ጭራሽ ወደዝዋይ ማረሚያ ቤት እያዛወራቸው ይገኛል፡፡ ወደዝዋይ ማረሚያ ቤት ማዛወሩ ቋሚ ቦታ እየተፈለገላቸው ከሆነ ይቅርታቸው ‹‹ተሰርዟል ወይም ተቀባይነት አላገኘም›› ማለት ስለሚሆን ይኸው ተገልጾ ሊነገራቸው በተገባ ነበር፤ ካልሆነም ደግሞ የቤተሰባቸውንም የፍርደኞቹንም ሕይወት በሚያመሳቅል ሁኔታ እያንገላቱ ጊዜ ከማባከ ቶሎ ፈትቶ ሕገ-መንግሥታዊ ስርዓትን ማስጠበቅ ተገቢ ይሆናል፡፡ አሁንም ቤተሰቦች ይጠይቃሉ፤ የዝውውሩ ምስጢር ምንድን ነው? ይቅርታ የጠየቁትስ የማይፈቱት ለምንድን ነው?

Friday, March 1, 2013

#Ethiopia: የአድዋ [ዕ]ድል


መቶ ዐሥራ ሰባት ዓመት ወደኋላ፤ መጀመሪያ (ከዚህም ዓመታት በፊት) አውሮጳውያን ኃያላን በበርሊን ያደረጉት ‹‹አፍሪቃን የመቀራመት›› ስምምነት ይቀድማል፡፡ ሁሉም የየራሳቸውን ሲወስዱ፣ ጣሊያንም ኢትዮጵያ (እና ሶማሊያ…) ደርሰዋት ነበር፡፡ የመጀመሪያው የጣሊያን ጦር በባሕርምላሽ (የአሁኗ ኤርትራ) በኩል ሲመጣ የወቅቱ የባሕርምላሽ ገዢ የነበሩት የራስ አሉላ እንግዳ (አባ ነጋ) ሠራዊት የጣሊያንን ሠራዊት ዶጋሊ ላይ በተደረገ ፍልሚያ ከ500 ወታደር 100 ብቻ በሕይወት አስቀርቶ መለሰው፡፡ ያኔ የጣሊያን ፓርላማ ተሰበሰበ፤ ተሰብስቦም አላበቃ በ332 ለ40 አብላጫ ድምፅ ወደኢትዮጵያ ተጨማሪ (5000ሺ ወታደር የያዘ) ሠራዊት ለመላክ ወሰነ፡፡

ከዚያ በኋላ ነው የውጫሌ ውል የተከተለው፡፡ ለጠነከረ ወዳጅነት እና ለጋራ ተጠቃሚነት በምኒልክ እና በጣልያን መልእክተኛ መካከል የተፈረመው የውጫሌ ውል ደግሞ አማርኛውና ጣልያንኛው አንድ ዓይነት ትርጉም ይኑረው ቢልም አንቀጽ 17 ‹‹ኢትዮጵያ የጣልያን ሞግዚት›› እንድትሆን በተዘዋዋሪ የሚያታልል ነበር፡፡ ትርጉሙ ሲነቃበት ዐጤ ምኒልክ ውድቅ ከማድረግ አልተመለሱም፡፡ እንግዲህ የአድዋ ጦርነት መነሻ የሚባለው ይህ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ ለኢጣሊያ የበርሊን ስምምነት ሽልማት መሆኗ ግን መሠረቱ ነው፡፡

ጦርነቱ ሲጀመር አገር ዘመተ፡፡ 80,000 ኢትዮጵያውያን ለጦርነቱ ሲወጡ ከነዚህ ውስጥ ቆመህ ጠብቀኝ ጠብመንጃ የታጠቁት ጥቂቶቹ ነበሩ፡፡ ሌላው ጦርና ጋሻውን እየሰበቀ ወጣ፡፡ በጣሊያን በኩል ደግሞ 18,000 ወታደሮች ተሰለፉ፡፡ የአገር ፍቅር፣ የጀግንነት እና የአትንኩኝ ባይነቱ ጦርነት ተጀመረ፡፡ ጀግኖች ተጋደሉ፤ በዕለቱ ጦርነት ማብቂያ ላይ የጣልያን ሠራዊት በአውሮጳውያን የቅኝ ገዢነት ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ እልቂት አስተናገደ፡፡ እስከ 7,000 የሚገመቱ የጣሊያን ወታደሮች ሞቱ፣ 3000 ያህል ተማረኩ፤ በኢትዮጵያ ወገንም 4,000 የሚጠጉ ተሰዉ፣ የቆሰሉት ደግሞ ከ10,000 በላይ ነበሩ፡፡ ድል ለኢትዮጵያ ሆነ፡፡

ፌሚኒዝም በኢትዮጵያ፦ የሚታደሉት ወይስ የሚታገሉት?

​( በፍቃዱ ኃይሉ ) ​ " እውነቱን ለመናገር፣ ከፌሚኒዝም ታሪክ ጋር የምጋራቸውም ሆነ የማልስማማባቸው ነጥቦች አሉኝ፤ [ ነገር ግን ] የሌለኝን ማዕረግ ወስጄ ራሴን [ ፌሚኒስት በሚ...