Wednesday, September 9, 2026

ፌሚኒዝም በኢትዮጵያ፦ የሚታደሉት ወይስ የሚታገሉት?

​(በፍቃዱ ኃይሉ)

"እውነቱን ለመናገር፣ ከፌሚኒዝም ታሪክ ጋር የምጋራቸውም ሆነ የማልስማማባቸው ነጥቦች አሉኝ፤ [ነገር ግን] የሌለኝን ማዕረግ ወስጄ ራሴን [ፌሚኒስት በሚል ሥም] ለማቆላመጥ አልፈልግም።" (የጀርመን የመጀመሪያዋ ሴት ቻንስለር አንጌላ መርኬል፣ እኤአ 2017 በበርሊን Women20 Summit ላይፌሚኒስት ነዎት ወይ?” ተብለው ሲጠየቁ የሰጡት መልስ።) 

"ያኔ ስናገረው ትንሽ እየፈራሁ ነበር። አሁን ግን በደንብ አስቤበታለሁ፤ በዚህ መልኩ ሲታይ ሁላችንም ፌሚኒስቶች መሆን አለብን ማለት እችላለሁ።" (አንጌላ መርኬል እኤአ 2021 "ሁላችንም ፌሚኒስት መሆን አለብን" በሚለው ንግግሯ/መጽሐፏ የምትታወቀው ናይጄሪያዊት ቺማማንዳ አዲቼ የተሳተፈችበት መድረክ ላይ ተመሳሳይ ጥያቄ ተጠይቀው የሰጡት ምላሽ።)

ፌሚኒዝም በኢትዮጵያ ውስጥ መጠነ-ሰፊ ማኅበራዊ ተፅዕኖ ማሳደር የመጀመሩን ያክል፣ የተቀናጀ የሚመስል ፅኑ ተቃውሞ እና ፍረጃም እየገጠመው ነው።

ነገር ግን በፌሚኒዝም ላይ የሚሰነዘሩ ነቀፌታዎች አዲስምአገር በቀል አይደሉም። ንቅናቄው ከተወለደበት ጊዜ ጀምሮ በየደረሰበት ማኅበረሰብ እና በየዘመኑ እየተፈተነ፣ እየወደቀና እየተነሳ እዚህ የደረሰ ኅያው ሞገድ ነው። እንዲያውም የሚገርመው፣ ፌሚኒዝምን በመተቸትና ድክመቱን በማጋለጥ ረገድ ከራሳቸው ከፌሚኒስቶቹ የከረረ ሂስ ያቀረበ ሌላ አካል የለም። የንቅናቄው ትልቁ ጥንካሬም ራሱን ከትችት በላይ አድርጎ ባለማኖሩ፣ ሁሌም ራሱን በመፈተሽ መታደስና ማደግ መቻሉ ነው።

ትርጉም፣ ሞገዶች እና የንድፈ-ሐሳብ ልዩነቶች

ፊሚኒስቶች ሁሉ አንድ ዓይነት የችግር አረዳድ፣ የመፍትሔ መንገድ እና የውጤት ዒላማ የላቸውም። ለዚህም ነው አንዳንድ ፌሚኒስቶችሊበራል ፊሚኒስትማርክሲስት ፌሚኒስትኢንተርሴክሽናል ፌሚኒስትክርስቲያን/ሙስሊም ፌሚኒስትሲሉ የምንሰማቸው። አንዳንዶቹ በአባውራ የሚመራው ቤተሰብየጭቆና መሸሸጊያ ነውና ይፍረስ(abolitionists) ሲሉ፣ ሌሎቹ ደግሞየለም፣ ይታደስ” (reformists) ይላሉ።

ፌሚኒዝም በኢትዮጵያ፦ የሚታደሉት ወይስ የሚታገሉት?

​( በፍቃዱ ኃይሉ ) ​ " እውነቱን ለመናገር፣ ከፌሚኒዝም ታሪክ ጋር የምጋራቸውም ሆነ የማልስማማባቸው ነጥቦች አሉኝ፤ [ ነገር ግን ] የሌለኝን ማዕረግ ወስጄ ራሴን [ ፌሚኒስት በሚ...