Monday, February 27, 2012

የአሜሪካ ኮንግረስ እና ሌሎችም ከኢትዮጵያ ፓርላማ መማር የሚገባቸው!


(የዓለማችንን ሕዳሴ ለማፋጠን የቀረበ ምክረ ሐሳብ) እስከዛሬ የጻፍኳቸው ሁሉ የግል አቋሜን የሚያንጸባርቁ አልነበሩም፡፡ ነገርዬዎቹ “ኪራይ ሰብሳቢ” የተባለ ሰይጣን ለክፎኝ የተናገርኳቸው ነበሩ፡፡ ሰይጣኑ የለከፋቸው ሰዎች በኢትዮጵያ የተገነቡት ፎቆችና መንገዶች፣ የሰፈነው መልካም አስተዳር፣ በ11.4% የሚመነደገው ኢኮኖሚ አይታያቸውም፡፡ ለነሱ የሚታያቸው ድንጋይ ሲወረውሩ÷ ፓሊሶች ራሳቸውን ለመከላከል በሚተኩሱት ጥይት የሚሞቱ አደገኛ ቦዘኔዎች፣ ከስንት አንዴ የሚገለበጡ የምርጫ ኮሮጆዎች፣ የመንግስትን ሕልውና በስክርቢቶና ወረቀት የሚያናጉ ጋዜጠኞች መታሰር፣ የኢኮኖሚውን ዕድገት ተከትሎ የተከሰተው የዋጋ ግሽበት ብቻ ነው፡፡

ቻይናዊው ዕውቅ ኮሚኒስትና የፖለቲካ ጠቢብ ኪል ሃንግ÷ ጥርነፋ ወከመ ለስልጣን በሚል ርዕስ በጻፉት መጽሃፋቸው ላይ በኪራይ ሰብሳቢ ሰይጣን የተለከፉ ዜጎች ነፃ ሊወጡ የሚችሉባቸውን መንገዶች ሦስቱ ‘መ’ዎች በማለት ሰይመዋቸዋል፤ እነሱም መጠመቅ፣ መታረም ወይም መሰደድ ናቸው፡፡

መጠመቅ፡- በሚባለው መንገድ ኪራይ ሰብሳቢዎች በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ዶክትሪን ከተሰበኩና ካመኑ በኋላ “የልማታዊ ዜግነት” ጠበል ተረጭተው (ተጠምቀው) ካለፈው ሃጢያታቸው ተሰርየው÷ ምቹ ወንበርና ስልጣን፣ በቂ ደሞዝና ጥቅማጥቅም አግኝተው በሰላም የሚኖሩበት ዕድል ይሰጣቸዋል፡፡ ያለፈው ሃጢያተቸውን ያነሳም “ውሾ ይሁን” ተብሎ ይረገማል፡፡ (በዚህ መንገድ እነ ሽመልስ ከማል፣ እነ ሬድዋን እና እኔ የዚህ ጠመቃ ተጠቃሚዎች ነን፡፡)

Friday, February 24, 2012

ኑሮ በአገርኛ÷ ጾም ይበዛበታል!


ባሕር ማዶ ካሉ ሰዎችጋ ስናወራ አንዳንድ የማይገቡን ወሬዎችን እየሰማን ጭንቅላታችንን እየናጥን “ወቸ ጉድ!” ማለታችን አይቀሬ ነው፡፡ ለኛ ባዳ ከሆነው ከቀላሉ “GPS” ጀምሮ፣ credit card ቢሉ፣ ምን ቢሉ ሁሉም ለኛ እንቆቅልሾች ናቸው፡፡ ወጉ ቀርቶብኝ በቅጡ በኮነነኝ እንዲሉ “GPS” ቀርቶብኝ እበላው ባገኘሁ የሚለው እስኪታወሰን ድረስ እንደመማለን፡፡ እዚህ GPS የለም፣ credit card የለም፣ ባቡር (ወይም subway station ብሎ ቋንቋ) የለም፣ smart phone የለም፣ wi-fi የለም (አለ እንዴ?) ለነገሩ የዚህ ጫወታ ጉዳዮች እነዚህ ሁሉ ስላልሆኑ እንኳን ደስ ያላችሁ፡፡ በርግጥ ግን ወደጫወታው አጀንዳ ለመድረስ አሁንም ዳር፣ ዳሩን መነካካት የግድ ነው፡፡ ‹አሜሪካኖች ለምን ወፋፍራም ሆኑ? ኢትዮጵያውያኖች ለምን ቀጫጭን ሆኑ?› ብለን ብንጀምርስ!

Friday, February 10, 2012

አማርኛ በመዝገብ ላይ


ዘፍጥረት 29÷11-16 (በግዕዝ)
በሚያውቁት ቋንቋ መናገር አንጀትን ያርሳል፡፡ ለዚህም ነው አንዳንዶቻችን በውጭ ቋንቋ፣ ከውጭ አገር ሰዎች አውርተን ስናበቃ ነፃ የመውጣት ስሜት የሚሰማን፡፡ ‘ሶሲዮሎጂስቶች’ ቋንቋን ከባሕል ገንቢ ወይም ገላጭ ቅንጣቶች መካከል ዋነኛ ሲሉ ያኖሩታል፡፡ የአንድ ማሕበረሰብ ባሕል እና ዕውቀት በቋንቋው ውስጥ ይገለጣል፡፡ ምንም እንኳን ቋንቋዎች ሁሉ ሙሉ ናቸው ብንልም÷ ባሕሉ የማያውቃቸው ብዙ ቃላቶች ግን እንደሚኖሩት መካድ አይቻልም፡፡ ለምሳሌ በአማርኛችን snow (‘ስኖው’) ለሚለው ቃል አንድም አቻ ትርጉም የለውም፡፡ በሰሜን አሜሪካ እና ሩሲያ መካከል፣ አላስካ አካባቢ የሚኖሩ የዚያው አካባቢ ጥንታዊ ሕዝቦች (እስኪሞዎች ይበላሉ) ስኖውን የሚወክሉ በርካታ ቃላቶች አሉዋቸው፡፡ ለምሳሌ አፑት ~ መሬት ላይ የተከመረ ስኖውጋና ~ እየዘነበ ያለ ስኖውፒቅሲርፖቅ ~ አየርላይ እየተንሳፈፈ ያለ ስኖውቂሙቅሱቅ ~ የስኖው ሰፈፍ፡፡

በሃገራችን አሁን ዘመን እየቀየረን መጣ÷ እንጂ ሴትን ለማማለል ገዳይነት ነበር የሚያስፈልገው፡፡ አንበሳ መግደል፣ ጠላትን በመግደል… ለዚህም ነው Romance ለሚለው ቃል ትርጉም (በአማርኛ) የማይገኝለት፡፡ ብቸኛው romanticነት ጀግንነት ነበርና፡፡ አብዛኛውን ኢትዮጵያዊ ወራጅ ወንዞች እንጂ ውቅያኖሶች አይጎራበቱትም÷ ለዚህ ነው በአማርኛ waterbank፣ shore፣ beach ለመሳሰሉ ቃላት ትርጉም ማግኘት የሚቸግረን፡፡ ይህ ዓይነቱ ችግር የአማርኛ ቃላቶችን ወደእንግሊዝኛ ልንመልስ ስንሞክርም ይገጥመናል፤ ችግሩ እንግሊዝኛው ላይ እርግጠኛ መሆን ስለሚቸግረን ይሄ፣ ይሄ ማለት ያስፈራናል፤ እላይ የተዳፈርነው የራስ መቼም የራስ ነው በሚል ብሒል ነው፡፡ ለምሳሌ፣ ‹ይሉኝታ› ለሚለው የአማርኛ ቃል የእንግሊዝኛ አቻ አንድ ቃል ፈልጌ አጥቻለሁ፡፡ ምናልባት አፈ-እንግሊዞቹ ይሉኝታ ስለማያውቁ ይሆን?

Thursday, February 2, 2012

የሐበሻ አምልኮ በኢትዮጵያ


(መግባቢያ፤ በዚህ ጽሁፍ ‘ሐበሻ’ ማለት ኢትዮጵያዊ፣ ‘አምልኮ’ ማለትም የተጋነነ አድንቆት የሚል ትርጉም ብቻ አላቸው፡፡) ‹የፈረረንጅ አምልኮበኢትዮጵያ› በሚል በጻፍኩት ጽሁፍ ተበሳጭተው÷ ጠንከር ያለ ነቀፌታቸውን ያደረሱኝ በርካቶች ናቸው፡፡ (በተለይም ethiopianreview.com ላይ!) የዚያን ቀጣይ ጽሁፍ በዚህ ርዕስ ለመጻፍ የተገደድኩት ያለፈው ጽሁፍ ስህተት መሆኑን አምኜ በተቃራኒው ለማረም ቢሆን ‹‹መልካም ነበር፡፡›› ግን አይደለም፤ ያም ሆነ ይህ ጽሁፍ ማሕበረሰባችንን መነቀፍ ባለበት ጉዳይ ለመንቀፍ የማይሳሱ ጽሁፎች ናቸው፡፡

በመጀመሪያ የቀደመው ጽሁፍ ለምን ነቃፊ በዛበት የሚል ጥያቄ ማንሳቱ ተገቢ መስሎ ይሰማኛል፡፡ የሁሉንም አስተያየት ሰጪዎች መልዕክት ያለምንም ማንገራገር በአንድ ጨፍልቆ መረዳት ይቻላል፡፡ ኢትዮጵያውያን ለባዕድ (ማለትም ለፈረንጅ) አምልኮ ወይም አድንቆ እጃቸውን የሰጡት ከመቼ ጀምሮ ነው በሚለው ጥያቄ ውስጥ እኔ መልስ ይሆናል ያልኩት ክርስትና ወደኢትዮጵያ መግባት ከጀመረ ወዲህ ነው የሚለውን ነው፡፡ ብዙዎች ክርስትና መነካቷን አይወዱምና የቁጣ ናዳ አወረዱብኝ ማለት ይቀላል፡፡ (ለጨዋታ ያህል ይሄ ጽሁፍ ‹‹ናዳን ለማቆም የተሮጠ ግለሰባዊ ሩጫ›› ነው ልንለው አንችላለን፡፡) እንዲያውም ክርስትና ለኢትዮጵያውያን የተሰፋ (ከባዕድ ያልወረስነው) እንደሆነ ሊያስረዱኝ የሞከሩ ሰዎችም አልጠፉም፡፡ ይሄ ሐሳብ ነው ወደዛሬው ጽሁፌ የሚያንደረድረኝ - የሐበሻ አምልኮ ብዬዋለሁ፡፡

Sunday, January 29, 2012

አፍንጫ ሲመታ ዓይን አያለቅስም ወይ?


አንድ የቆየ ቀልድ አስታውሳለሁ፡፡ ኒው ዮርክ ውስጥ አንዲትን ሕፃን ልጅ ውሻ ሲያባርራት ያየ አንድ ሰው ውሻዋን በያዘው አጠገቡ ባገኘው ዱላ መትቶ ይገድልና ልጅቷን ያድናታል፡፡ ይህንን ይመለከት የነበረ አንድ ጋዜጠኛ ወደሰውየው ይቀርብና ‹‹እሺ፤ ጀግናው አሜሪካዊ - እስኪ የልጅቷን ሕይወት እንዴት እንዳተረፍክ ንገረኝ?›› ሰውየው ‹‹ኧረ እኔ አሜሪካዊ አይደለሁም›› አለ፡፡ ‹‹እሺ፤ ጀግናው የኒው ዮርክ ሰው..›› ብሎ ጋዜጠኛው ሊቀጥል ሲል÷ ሰውየው ‹‹ኧረ የኒው ዮርክም ሰው አይደለሁ፤ ለጉብኝት ነው የመጣሁት›› ይለዋል፡፡ ጋዜጠኛው ፈገግ ብሎ ‹‹ታዲያ የምን አገር ሰው ነህ?›› ሲል ይጠይቃል፡፡ ሰውዬው ‹‹የሳውዲ አረቢያ›› ሲል ይመልሳል፡፡ በማግስቱ የኒው ዮርክ ጋዜጦች ‹‹አንድ አክራሪ ኢስላሚስት በኒውዮርክ ከተማ ውስጥ ውሻ ቀጥቅጦ ገደለ›› የሚል ዜና ይዘው ወጡ፡፡

ጆርጅ ቡሽ በዘመናቸው ከሰሯቸው ስህተቶች በሙሉ የከፋ ሊባል የሚችለው በሽብርተኞች ላይ ባወጁት ዘመቻ ‹‹ሽብርተኛ›› ማለት ‹‹ሙስሊም›› ማለት እንዲመስል ማድረጋቸው ነው፡፡ ይህንን ለማስተባበል መንግስታቸው ቢደክምም ተሳክቷል ማለት አይቻልም፡፡ ብዙዎች የተወናበደ አመለካከት አፍርተው ቀርተዋል፡፡ በዚህ ብስጭት ሃይማኖታዊ ሕልውናቸውን ለማዳን የፈለጉ የሚመስሉ ምስኪኖች አልቃይዳን ለመደገፍ ተገድደዋል፡፡

አሜሪካ የምታደርገው ማናቸውም ነገር በሌላው ዓለም ላይ ተፅዕኖ ማሳደሩ አይቀርም፡፡ ሉላዊነት (globalization) ባመዛኙ አሜሪካዊነት (americanization) መሆኑን ብዙዎች የሚስማሙበት ሐቅ ነው፡፡ የአሜሪካ ተጽዕኖ ለሁሉም የዓለም አገራት ይዳረሳል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥም ይሄ ተጽዕኖ ይንፀባረቅ ይሆናል የሚለው ስጋት ለብዙዎቻችን ልብ የሚያርድ ጉዳይ ነው፡፡

Friday, January 27, 2012

የኢትዮ ቴሌኮም ቁልቁለት

ፎቶ፤ www.stockphotopro.com

ሐሙስ ዕለት አመሻሹ ላይ ስልኬ ካርዱን ጨርሶ የጀመርኩትን ወሬ አቋረጠኝ፡፡ ወዲያው ካርድ ገዛሁና ሞልቼ ወሬዬን ለመቀጠል ተጣደፍኩ፡፡ ምን ዋጋ አለው? አዲሱ *805* የካርድ መሙያም ሆነ የቀድሞው 904 ገንዘቤን ሊቀበሉኝ አልቻሉም፡፡ ብስጭቴ እየተጋጋለ ደጋግሜ ስሞክር አመሸሁ፤ አልተሳካም፡፡ በማግስቱ ካርዱን ለወሬው የማድረስ ሕልሜ አልቆ፣ ገንዘቤን ከኪሳራ ለማዳን ማለዳ ጀምሬ መቀጥቀጤን ቀጠልኩ÷ በቀላሉ የሚሆን አልነበረም፡፡ በመጨረሻ እኩለ ቀን ሲቃረብ 805 – “Sorry, the operation failed. Bye” የሚለውን የተለመደ ጽሁፍ ካስነበበኝ በኋላ÷ ካርዴ እንደተሞላ የሚነግር አጭር የጽሁፍ መልዕክት ደረሰኝ፡፡ ደስ አለኝ ልበል?! ደስ ሊለኝ ግን አይገባም፤ ምክንያቱም ፍዳዬን ሳይ አድሬ ያረፈድኩት በኔ ጥፋት ሳይሆን በቴሌኮሙ የቴክኒክ ድክመት ነው፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም ከየት ወዴት?
የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን የስንት ዓመት ስሙን በጥላ ቢሱ ኢትዮ ቴሌኮም የቀየረው የለውጥ ርምጃ የሚጀምረው በስም ለውጥ ነው ከሚል መርኅ ይመስላል፡፡ የራሱን የሚመስል ስም ያጎናፀፈው ፍራንስ ቴሌኮም ቴሌን ማስተዳደር ሲጀምር÷ የተጣለበት ተስፋ (ትርፍ መጨመር ቢሆንም) የተዘበራረቀውንና ዘመናዊነት የጎደለውን አሠራር እንዲያፀዳ በማሰብም ጭምር መሆኑም ይታወቃል፡፡ ግን እየሆነ ያለው የተባለው ነገር ነውን?

ፈረንሳዊው አስተዳደር ሥራውን አሀዱ ያለው የሞቱና ድርጅቱን የለቀቁ ሠራተኞን በኃላፊነት ቦታዎች በመመደብ ነበር፡፡ በርግጥ ያንኛው ለዚህንኛው ሲያስረክብ የተፈጠረ ስህተት ነው ተብለን አምነን ነበር፤ እየቆየን እየተመለከትን ያለነው ግን የዛኔውን እምነታችንን ዛሬ ላይ ቆመን እንድንጠራጠረው የሚያስገድድ ነገር ነው፡፡

Tuesday, January 17, 2012

የፈረንጅ አምልኮ በኢትዮጵያ

ፈረንጅ የሚለው ቃል÷foreign ከሚለው እንግሊዝኛ ቃል የመጣ ይመስለኛል፡፡ ምናልባትም አባቶቻችን foreign የሚለውን እንግሊዝኛ ፈረንጅ ብለው ሳያነቡት አይቀርም፡፡ በዚህ ዓይነት ፈረንጅ ማለት ኢትዮጵያዊ ያልሆነን ሰው ይወክላል ማለት ነው፡፡ እኔ ግን በርዕሴ ፈረንጅ ብዬ የጠቀስኩት ነጮችን መሆኑን ተገንዘቡልኝ፡፡

የፈረንጅ አምልኮ በኢትዮጵያ መኖሩን ሳናውቅ ስር ሰዶ ከርሟል፡፡ ምንም እንኳን ጉዳዩ ቅርጫፉን የዘረጋው አሁን ቢሆንም÷ ከጥንት የተጀመረ አምልኮ ስለመሆኑ የታሪክ ድርሳናትን በመመርመር መረዳት ይቻላል፡፡

የፈረንጅ አምልኮ ድሮ
የፈረንጅ አምልኮ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጣባን ክርስትና እና እስልምና ወደኢትዮጵያ በገቡበት ዘመን እንደሆነ አምናለሁ፡፡ ይሄ ብዙዎችን የሚያናድድ አስተሳሰብ ቢሆንም÷ እኔን ግን ከማሳመን አላለፈም፡፡ ምክንያቱም ኢትዮጵያውያን ሀገር በቀል እምነቶችንና ስልጣኔዎችን ደምስሰው ባዕዳን ሃይማኖቶችንና ስልጣኔዎችን የተቀበሉት በነዚያ ጊዜያት ነው፡፡

The Return to Rule by Law: The Case of Draft CSO Law in Ethiopia

(Befekadu Hailu) [The original version of this piece is written in Amharic; please read the Amharic version for accuracy.] The Ministry...