Showing posts with label Amharic Language. Show all posts
Showing posts with label Amharic Language. Show all posts

Monday, August 8, 2016

ቋንቋችንን እንታዘበው

በፍቃዱ ኃይሉ

፩. Independence, Freedom, Liberty (ነጻነት የቱ ነው? የቱስ አይደለም?)

"ነጻነት ውስብስብ ነው" ብዬ ልጀምር።ነጻነትየሚለውን የአማርኛ ቃል በተለምዶ ከላይ የዘረዘርኳቸውን ሦስቱንም የእንግሊዝኛ ቃላት ለመተርጎም እንጠቀምበታለን። ትርጉሙ ግን ሁሌም አጥጋቢ አይሆንም።

ቃላት ባብዛኛው ደረቅ አይደሉም ፅንሰ-ሐሳብ (concept) ያዝላሉ። የሆነ ፅንሰ-ሐሳብን የሚወክሉ ቃላቶች በሆነ ቋንቋ ውስጥ የሉም ማለት የዚያ ፅንሰ-ሐሳብ በቋንቋው ተናጋሪው ማኅበረሰብ ዘንድ እምብዛም አይታወቅም እንደ ማለት ነው። ፅንሰ-ሐሳቡን በቃላት ቀንብቦ ማስቀመጥ መቻልና ብዙኃን በየለት ንግራቸው እንዲጠቀሙበት ማድረግ መቻል ቃሉን ከነፅንሰ-ሐሳቡ በማኅበረሰቡ ውስጥ ማስረፅ ማለት ነው። ይህንን ለማስረዳት ቀላሉ መንገድ የአየር ሁኔታን መግለጽ ነው። በረዶ (Ice) እና snow (የበረዶ ብናኝ እንበለው) ሁለት የተለያዩ ነገሮች ናቸው፤ በአማርኛ ግን የሚጠሩት በአንድ ሥም - በረዶ - ተብለው ነው። Frost (snow ወይም የበረዶ ብናኝ የለበሰ ተራራ) አመዳይ ይባላል። በአገራችን የሌለ በመሆኑ ሥሙ የውሰት እና እምብዛም የማይታወቅ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ (መዝ 147: 16) ከመገኘቱ በቀር ቃሉም፣ ሐሳቡም በማኅበረሰቦቻችን ዘንድ የሌለ ነገር ነው። Tornado የሚለው ቃል የአማርኛ አቻ የለውም፤ ምክንያቱም በሐሳብ ደረጃም እምብዛም አይታወቅም። ሩቅ ምሥራቃውያን በየጊዜው ለሚያጠቃቸው የነፋስ እና የማዕበል ዓይነት (ነፋስን ከነፋስ፣ ማዕበልን ከማዕበል) የሚለዩባቸው እልፍ ቃላት አሏቸው። የቃላት እና ሐሳብ ቁርኝት እንዲህ ይገለጻል።

ኢትዮጵያ ውስጥነጻነትየሚለው ቃል እና ፅንሰ-ሐሳብ በአማርኛ ተናጋሪው ዘንድ እንዴት ነው እየታየ ያለው? መነባንቡ (rhetoric) ብቻ ነው ወይስ ግንዛቤውም አብሮት አለ? አብረን እንፈትሽ።

ምሳሌ ፩፦

A) Ethiopia is an independent country.
B) Zone 9 is an independent blogosphere.
C) She is an independent woman.

በሚሉት ሦስት /ነገሮች ውስጥ ‘independent’ የሚለው ቃል ሦስት ተለምዷዊ ትርጉሞች አሉት፣

) ኢትዮጵያ "ነጻ" አገር ናት።
) ዞን ነጻየጡመራ መድረክ ነው።
) እሷነጻሴት ናት።

ሦስቱ ቃላቶች በዐውድ (context) የተለያዩ ቢመስሉም በመሠረታቸው አንድ ናቸው። ሁሉም፣ማንም ላይ ጥገኛ ያልሆነ/ወይምራሱ/ሷን የቻለ/የሚለውን ሐሳብ ያዘሉ ናቸው። ነገርዬው በራስ ጉዳይ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ወይም በሌሎች ጉዳይ ላይ አቋም ለመያዝ የማንም ተፅዕኖ የሌለበት እንደማለት ነው። መቶ በመቶ ራስን መቻል ወይም ከሌሎች ተፅዕኖ መላቀቅ የሚባል ነገር አለ ብዬ ባላምንም የሌሎችን በራስ ጉዳይ ጣልቃ ገብነት በእጅጉ መቀነስ መቻልንራስን መቻልብለን ብንጠራው አይከፋኝም። በላይኞቹ ምሳሌዎች ላይ ‘independence’ ራስን መቻል ወይም ገለልተኛ የሚሉት ቃላቶች ሊተኩት ይችላሉ።

Sunday, December 1, 2013

#16Days: የቃላት ጥቃት ጠባሳው አይሽርም!



ሰዎችን ለማድነቅ የምንጠቀምበት ቃል ‹ወንድ› ወይም ‹ወንዳታ› በሆነበት ማኅበረሰባዊ አስተሳሰብ የምትደነቅ ሴት ማብቀል ይከብዳል፡፡ የምትደነቅ ሴት ብትበቅል እንኳ የማኅበረሰቡ ውጤት ነው ማለት አይቻልም ባይ ነኝ፤ የግል ጥረቷ ውጤት ነው የምትሆነው!

ቋንቋ፣ አባባሎች እንዲሁም ተረትና ምሳሌዎች ማኅበረሰቡ አባላቱን የሚያሳድግበትን (nurture የሚያደርግበትን) መንገድ ያሳብቃሉ፡፡ ያልዘራነውን አናጭድም፤ ስለዚህ አጋጣሚውን ተጠቅመን ከቃላት አጠቃቀማችን ጀምሮ ራሳችንን መገምገም መጀመር ሊኖርብን ነው፡፡

ለመሆኑ የአማርኛ ተረትና ምሳሌዎቻችን ስለሴት ምን ይላሉ?

Saturday, January 5, 2013

እነዚህን አንብባችኋቸዋል?

በዚህ ጦማር ላይ ከጻፍኩ ሰነበትኩ:: ነገር ግን ብዙዎቻችሁ እንደምታውቁት የጠፋሁት መጻፍ እርም ብዬ ሳይሆን ዞን ዘጠኝ ላይ መጻፍ በመጀመሬ ነው:: ታዲያ ምናለ ይሄንን subscribe አድርገው ዞን ዘጠኝን ያላደረጉ ካሉ ቢያነቡኝ ብዬ ጥቂቶቹን እንዲህ ዘረዘርኳቸው:: እንዳሻችሁ አድርጓቸው::


15. የሥርዐት ለውጥ እና ሃይማኖቶች

14. ለውጥን መቋቋም እና መፍራት

13. አብዮት ወይስ አዝጋሚ-ለውጥ?

12. ግልጽ ደብዳቤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ

11. በኢትዮጵያ የቡድን አመራር ተጀምሯል?

10. የጉዞ ማስታወሻ፤ ሥልጣኔ ወደላይ እና ወደታች

9. የጉዞ ማስታወሻ፤ መቐለን በአንድ ቀን

8. ኢሕአዴግ ሥልጣኑን በምርጫ ይለቃል?

7. ጠንቅቆየመጻፍና አለመጻፍ ጉዳይ

6. የእነርሱ እና የእኛ ሕዳሴ

5. የታክሲ ሰልፍ መጀመሪያውና መጨረሻው

4. ‹‹ሕዝብ›› ምንድን ነው?

3. የትችት ባሕላችንን ብንተቸውስ?

2. ይቅርታ የሚገባው የኢትዮጵያ ሕዝብ!

1. አራማጅነትበኢትዮጵያ



Transforming Ethiopia’s Exclusionary Constitution into an Inclusive One

Before introducing my proposal, I would like to explain my motivation for writing this now. One of the outcomes of the National Dialogue o...