Pages

Monday, July 25, 2016

“ጨዋ” ነዎት “ባለጌ”?



በፍቃዱ ኃይሉ*

ሐምሌ 27/2007 ለኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች እና ቀናኢ-ፍትሕ ለሆኑ ሰዎች በሙሉ የመርዶ ቀን ነበር፡፡ ስለ ሠላማዊነታቸው የተመለከታቸው በሙሉ የፈረደላቸው፣ ባንድ ወቅት መንግሥትም በወኪሉ በኩል ሲደራደራቸው የነበሩ፣ ለሦስት ዓመታት ያክል በሕግ የበላይነት አምነው ችሎት ፊት የሠላማዊነታቸውን ማስረጃ ሲደረድሩ የቆዩት (በተለምዶ በሚጠሩበት ሥማቸው) የሙስሊሞች ጉዳይ መፍትሔ አፈላላጊኮሚቴዎችእስከ 22 ዓመት የሚድረስ የፅኑ እስራት ፍርድ ተጣለባቸው፡፡ ይህንን ዜና የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢብኮ) 730 የቀን ዜና እወጃው ጀምሮ ሲለፍፈው ነበር፡፡ ከዜናው ጋር በማነፃፀሪያነት የቀረበው ሌላ ዜና ግን ግቡን ስላልመታ ይመስላል ማታ አልተደገመም፡፡ ያልተደገመው ዜና በተመሳሳይ አንቀፅ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ስለተፈረደባቸው ሰዎች ነው፡፡ እነዚህኞቹ መሣሪያ ታጥቀው የተወሰኑ ሰዎችን ገድለዋል፡፡ ሆኖም እንደ ኢ.ብ.ኮ. ዘገባየቅጣት ማቅለያ በማስገባታቸው” 14 ዓመት ተፈርዶባቸዋል፡፡ ዜናዎቹን ያዳመጡ ሰዎች ግን ማነፃፀር የቻሉት የሠላማዊነት ቅጣት መክበዱን ነበር፡፡

ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ “Military and militarism in Africa: the case of Ethiopia” ባሰኙት ጥናታቸው ላይ እንዲህ ይላሉ፡-

“በመካከለኛውዘመን እንዳየነው [ጨዋ] ማለት መሣሪያ ታጣቂ ማለት ነበር፡፡ ኋላ ላይ ግን ትርጉሙ ተለውጦ መልካም ፀባይ ያለው ማለት ሆነ፡፡ በተመሳሳይ፣ የቃሉ ተቃራኒ የሆነውባለጌየሚለው ቃልም የሚወክለው ጭሰኛውን (ማለትም መሣሪያ የማይታጠቀውን) ነበር፡፡ አሁን የዚህም ቃል ትርጉም ተለውጦ መጥፎ ፀባይ ያለው ማለት ሆኗል፡፡” (እራሴው እንደተረጎምኩት)

እንግዲህ ኢሕአዴግም የሚያስበው በቀደመው ዘመን ጨዋእናባለጌትርጉም ነው ማለት ነው፤ ለእርሱ መሣሪያ ከታጠቀ ይልቅ ሠላማዊ ይባልግበታል፡፡ (‹ይባልግበታልበአሁኑ ትርጉም!) ስለዚህ አቀጣጡም በዚያው መሠረት መሆኑን መግቢያ አንቀፁ ያመለክታል፡፡

የአሁኒቱ ኢትዮጵያ ገዢዎች (‹አመራሮችአላልኩም፤ አይመጥናቸውም) የመንግሥትን ሥልጣን ከተቆጣጠሩበት ጊዜ አንስቶ እስከ አሁን (ለሁለት ዐሥርት ዓመታት) ሠላማዊ ትግሎችን በፅኑ ተቃውመዋል፡፡ እንዲያውምየሚችለን ካለ በትጥቅ ትግል ይሞክረንየሚል መፈክር በተደጋጋሚ አስደምጠዋል፡፡ ዓላማቸው ግልጽ ነው፡፡ ያዋጣናል፣ እናሸንፍበታለን የሚሉትን የትግል ሜዳ እየመረጡ ነው፡፡ የኢሕአዴግ ተቃዋሚዎችስ? ገዢው በመረጠላቸው ሜዳ (battlefield) ቢገጠሙት ይሻላል ወይስ ሠላማዊነትን የሙጥኝ ቢሉ? የትኛው ያዋጣል? የትኛው ይቀላል? ከሕወሓት ምን መማር ይቻላል? አምባገነኖች እንዴት ሥልጣን ላይ ይሰነብታሉ?

ለነዚህ ጥያቄዎች መልስ ከመፈለጌ በፊት ነገሩ ሁሉ ለለውጥ ነው እና በዚህ ጽሑፍ ውስጥለውጥየሚባለውን ነገር ልበይን፡፡ለውጥማለት በዚህ አገባቡወደ ሕዝባዊት፣ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ የሚደረገው ሽግግርነው፡፡


አመፃዊ የትግል ስልት ያዋጣል?

ሠላማዊ ያልሆነ ትግል በሙሉ የትጥቅ ትግል አይደለም፡፡ አመፃዊ የሚለውን ቃል የተጠቀምኩት ከትጥቅ ትግል ወዲያ ሠላማዊ የማይባሉ ስልቶችንም እንዲያካትትልኝ ስለፈለግኩ ነው፡፡ በዚህ መስፈርት አመፃዊ ትግል በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ፣ ከአገሪቱ ታሪካዊ ሁነትም፣ ከዓለምቀፍ ተሞክሮዎችም በመነሳት ያዋጣል ወይ የሚልውን እንጠይቃለን፡፡ ለዚህ ጥያቄ በዚህ ጽሑፍ ሰጥቼ የማልፈው ጉዳይ በተነሳ ቁጥር የሚመጡልኝን መልሶች ነው፡፡